Sunday 30 December 2012

በሱዳን በኩል የሚካሄደው ሕገወጥ ንግድ እየተባባሰ መምጣቱ ተጠቆመ

ኢትዮጵያ ከሱዳን ጋር በሚያዋስናት ጠረፍ በኩል ሕገወጥ የገቢና ወጪ ንግድ መስፋፋቱን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ምንጮች ገለጹ፡፡ ኢትዮጵያ ከሱዳን በኩል የምትዋሰንባቸው ጋምቤላ፣ ቤኒሻንጉል ጉምዝና አማራ ክልሎች ውስጥ በሚገኙ የጠረፍ ከተሞች በርካታ ሸቀጦች፣ የቁም እንስሳት፣ ደንና የደን ውጤቶች በገፍ እንደሚወጡ ታውቋል፡፡

በቤንሻንጉል ጉምዝ በከፍተኛ ደረጃ የሚወጣውን የቁም እንስሳት ከፍተኛ መጠን ያለው የቁም ከብት አሁንም በጉባ በኩል እየወጣ መሆኑ ይነገራል፡፡ በተጨማሪም በጋምቤላና በቤንሻንጉል ጉምዝ በኩል ቡና በብዛት ከአገር እየወጣ እንደሚገኝ ተጠቁሟል፡፡ በአማራ ክልል መተማ በኩል የደን ውጤቶችና የቁም እንስሳት በከፍተኛ መጠን ከአገር እንደሚወጡ ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡

እነዚህን ሸቀጦች ለማስወጣት ለጭቃና ለጎርበጥባጣ መንገድ የማይበገሩ መርሰዲስ ከባድ የጭነት ተሽከርካሪዎች ጥቅም ላይ ይውላሉ፡፡ የጠረፍ ንግድ በተለይ ሥጋ ላኪዎችንና የቆዳ ፋብሪካዎችን እየጎዳና ከገበያ እያስወጣ እንደሆነ ይናገራል፡፡ ምክንያቱም ከጠረፍ ወደ መካከለኛው ገበያ መቅረብ የነበረበት የቁም ከብት በድንበር በኩል በሕገወጥ መንገድ እየወጣ በመሆኑ ነው፡፡

የዘርፉ ሕጋዊ ነጋዴዎች ይህንን ችግራቸውን በተደጋጋሚ ለመንግሥት ቢያቀርቡም፣ ጉዳዩ እየተወሳሰበ እንጂ መፍትሔ ማግኘት አለመቻላቸውን ይገልጻሉ፡፡

Saturday 29 December 2012

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሴራውን ጀመረ

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በሚያዝያ ለሚደረገው የአዲስ አበባና የአካባቢ ምርጫ ፓርቲዎች የውድድር ምልክት የሚወስዱበትን ጊዜ በሁለት ቀናት እንዳራዘመ ሲገልፅ ፓርቲዎች በበኩላቸው የውድድር ምልክት መውሰጃ ቀነ ገደብ አልነበረውም አሉ፡፡ ምርጫ ቦርድ ከትናት በስቲያ ፓርቲዎችን ለውድድር ለማነሳሳት በሚል የውድድር ምልክት የሚወስዱበትን ጊዜ በሁለት ቀን በማራዘም ዛሬ ታህሳስ 20 ቀን 2005 ዓ.ም ድረስ በቦርዱ ፅ/ቤት በመገኘት ምልክታቸውን እንዲወስዱ ጥሪ አቅርቧል፡፡

የምርጫ የጊዜ ሰሌዳውን በተመለከተ ከምርጫ ቦርድ ጋር መወያየት እንደሚፈልጉ ሲገልፁ የቆዩት 33ቱ ፓርቲዎች ምርጫ ቦርድ ያስቀመጠውን የጊዜ ቀነ ገደብ እንደማይቀበሉት የገለፁት  ቀነ ገደቡ ፓርቲዎችን እርስ በርስ ለመከፋፈልና ለመለያየት የሚደረግ ሴራ ነው ብለዋል፡፡

በምርጫው የጊዜ ሰሌዳ ላይ አለመስማማታችንና በምርጫ ምልክቱ ዙሪያ ውይይት እያካሄድን እንደሆነ ምርጫ ቦርድ ያውቃል ያሉት አቶ አስራት፤ ቀን ገደብ ማስቀመጥ የቦርዱ ስልጣንና ሃላፊነትን አይደለም ብለዋል፡፡ ቦርዱ የውድድር ምልክቱን ቀነ ገደብ ያስቀመጠው ለምርጫው አስቦ ሳይሆን ፓርቲዎችን ለመከፋፈል እንደሆነ አቶ አስራት ተናግረዋል፡፡

Sunday 23 December 2012

በኩዌት በሳዑዲ ዓረቢያና ጅዳ የኢትዮጵያ ኤምባሲ የሰው ኃይልን በርካሽ ዋጋ ሊያቀርብ እንደሚችል በአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ማስታወቂያው እያስነገረ ነው፡፡

Hellen Zewdu
 
ሰው በፈለገበት ቦታና አገር የመዘዋወር መብቱ በሕገ መንግሥቱ ተረጋግጦለታል፡፡ በኮንትራት በቤት ሠራተኝነት ወደ አረብ አገሮች የሚሄዱ ኢትዮጵያዉያን የሚደርስባቸዉ በደል ከጊዜ ወደ ጊዜ መባባሱ ይሰማል።   ኢትዮጵያውያኑ ላይ ከፍተኛ  የሆነ አካላዊና ሥነ ልቦናዊ  ጉዳት እየደረሰ ነው። ለዚህም በዋነኛነት ማሳያ የሚሆነው በተለያዩ የዓረብ አገሮች በቤት ሠራተኛነት በሚሄዱት እህቶቻችን ላይ የሚታየው የሞት፣ የአካል መጉደል፣ የመደፈርና ያለደመወዝ ማባረር ጥቂቶች ናቸው፡፡ በዚህ ዓመት እንኳን ከዓለም ደቻሳ ጀምሮ  በድብደባ ህይወታቸውን ያጡትን  ለከፍተኛ የአካል ጉዳት የተዳረጉትን የተደፈሩትን ከፎቅ የተወረወሩትን ለአእምሮ መቃወስ የተዳረጉት የትየለሌ ናቸው ኢትዮጵያዉያን የኮንትራት ሰራተኞች በአሰሪወቻቸው የሚደርስባቸውን ጥቃት ታዋቂ የሳዉዲ ጋዜጦች ሳይቀሩ በዝርዝር እየዘገቡት ነው፡፡

የወገኖቻችን እንግልት የሚጀምረው አገራቸው ላይ ነው፡፡ የሳዑዲ ዓረቢያ ዜግነት ያላቸው ኢትዮጵያውያንም በዜጎቻችን ላይ ክብራቸውን ጭምር የሚነካ ተግባር የሚፈጽሙ አሉ፡፡ በተለያዩ የአገሪቱ ክልሎች በደላላዎች እየተደለሉ ከየቀያቸው እየተፈናቀሉ ዜጎቻችን ለጉዳት እየተዳረጉ ነው፡፡ ሁሉም ነገር አልጋ ባልጋ እንደሆነና ወርቅ ተነጥፎ እንደሚጠብቃቸው በመስበክ ወጎኖቻችንን እያስጨረሱ ነው፡፡ ከእነዚህ ደላሎች በስተጀርባ የመንግስት እጅ አለበት መንግሥት ዜጎችን ከመጠበቅና ካለበት ኃላፊነት አንጻር እሱም ተጠያቂ ነው፡፡ ዕድሜያቸው እንዳልሞላ እየታወቀ ከ13-15 ዓመትን ልጅን 23-26 ዓመት በማለት  በማጣራትና አይቶም መገመት ሲቻል ፓስፖርት ይሰጧቸዋል የሚያስደነግጥ ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ወደ ሳዑዲና ኩዌት ለመሄድ የሚመጡት መጻፍ፣ ማንበብ የማይችሉና መታወቂያና ፓስፖርት መሆኑን መለየት የማይችሉ ናቸው፡፡ ፓስፖርት እስከሚያወጡና የሕክምና ምርመራ እስከሚደረግላቸው ድረስ ብዙ ችግሮችን ያሳልፋሉ ሁሉም ነገር ተሳክቶላቸው እስከሚሄዱ ድረስ የደላሎቹ የወሲብ መፈጸሚያ ይሆናሉ፡፡ የጤና ምርመራ ሲደረግላቸውም የHIV ተጠቂ ሆነው ይገኛሉ ውጤታቸው ሲነገራቸው እንደ ውርደት ስለሚቆጥሩት ተመልሰው ወደቀያቸው መግባትን ይተዉና ራሳቸውን በመሸጥ ለመተዳደር ይሞክራሉ፡፡ በሽታውንም ያስተላልፋሉ ላልተፈለገ እርግዝና ለ አደንዛዥ ዕፆች ተጋላጭ እየሆኑ ነው፡፡

Saturday 22 December 2012

ቅ/ሲኖዶስ የሠየመው የፓትርያሪክ አስመራጭ ኮሚቴ ዓለም አቀፍ ተቃውሞ ቀስቅሷል

ዕርቀ ሰላሙ ይቅደም›› የሚሉ ጳጳሳት የሲኖዶሱን ውሳኔ አንቀበለውም ብለዋል

የላሊበላው ውዝግብ ወደ አላስፈላጊ ግጭት እንዳያመራ ተሰግቷል

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የስድስተኛውን ፓትርያሪክ ምርጫ ዝግጅት የሚመራና እስከ ጥር መጨረሻ ዕጩዎችን የሚያቀርብ አስመራጭ ኮሚቴ መሠየሙ በቤተ ክርስቲያኒቱ ካህናትና ምእመናን ዘንድ ዓለም አቀፍ ተቃውሞ መቀስቀሱ ተገለጸ። ‹‹የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ያገባኛል›› በሚል መርሕ በዋናነት በማኅበራዊ ሚዲያዎችና ብሎጎች እየተገለጸ ያለው ይኸው ተቃውሞ፤ የቤተ ክርስቲያን ሰላምና አንድነት የሚረጋገጥበት የዕርቁ ጉባኤ ‹‹የአባቶች ጉዳይ ብቻ አይደለም፤ ምእመናኑን ያገለለ ሊኾን አይገባም›› በሚል የካህናቱና ምእመናኑ ድምፅ እንዲደመጥ የሚወተውት ነው፡፡

የቅ/ሲኖዶሱ አባላት የኾኑ ሊቃነ ጳጳሳትን ጭምር ያካተተው የዚህ ተቃውሞ መነሻ÷ የአስመራጭ ኮሚቴው መቋቋም በሀገር ውስጥ በሚኖሩትና በውጭ አገር በስደት በሚገኙት አባቶች መካከል ለሚካሄደው የዕርቀ ሰላም ውይይት መሰናክል ይኾናል በሚል ነው፡፡የቅ/ሲኖዶሱ የዕርቀ ሰላም ልኡክ በመኾን ወደ አሜሪካ ከተጓዙትና በዳላስ ቴክሳስ ከኅዳር 26 - 30 ቀን 2005 ዓ.ም በሰላምና አንድነት ጉባኤ አመቻችነት በተካሄደው የዕርቀ ሰላም ውይይት ላይ የተሳተፉት የደቡብ ወሎ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አትናቴዎስ ከትናንት በስቲያ ምሽት ለአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ በሰጡት አስተያየት÷ ቅ/ሲኖዶሱ እንደላካቸውና በሰላሙ ጉዳይ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተነጋገሩ ‹‹ስንዝር ያህል መራመዳቸውን›› ገልጸዋል፡፡ የዕርቀ ሰላም ልኡካኑ ይህን እያደረጉ ባለበት ኹኔታ ስለ ፓትርያሪክ ምርጫ መወያየትና አስመራጭ ኮሚቴ ማቋቋም ‹‹ኾኗል ብለን አናምንበትም፤ ኾኖ ከተገኘ ግን አንቀበለውም፤ እንቃወመዋለን›› ብለዋል - በቅ/ሲኖዶሱ ውሳኔ ቅር የተሰኙት ብፁዕ አቡነ አትናቴዎስ፡፡

በሰሜን አሜሪካ የዋሽንግተን ዲሲ እና ካሊፎርኒያ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል በበኩላቸው÷ የጥቅምት ቅ/ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ የወሰነው የፓትርያሪክ ምርጫ ሕገ ደንብ ተዘጋጅቶ የአሁኑ ስብሰባ እንዲጠራ እንጂ አስመራጭ ኮሚቴ ማቋቋም አዲስ ሐሳብ መኾኑን ለሬዲዮው በሰጡት ቃለ ምልልስ ተናግረዋል፡፡ በጥር ወር አጋማሽ በካሊፎርኒያ ሎሳንጀለስ ቀጣይ የሰላም ጉባኤ ለማካሄድ ቀጠሮ መያዙን ያስታወሱት ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል፤ የኮሚቴው መቋቋም የዕርቁን ሂደት እንዳያበላሸው ስጋት እንዳላቸው በመግለጽ ቅ/ሲኖዶሱ ከዕርቀ ሰላም ጉባኤው በፊት ሰፋ ያለ ሥራ ከማከናወን እንዲከለከል አሳስበዋል፡፡

Friday 21 December 2012

የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል” የምሥረታ መግለጫና ሃገራዊ ጥሪ

ታህሳስ 11 2005

የወያኔን ዘረኛና አምባገነን አገዛዝ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጫንቃ ላይ በትጥቅ ትግል ለማስወገድ “የግንቦት7 ሕዝባዊ ኃይል” የሚል ስያሜ የሰጠነውን፣ በሃገር ወዳድና ለህዝብ ተቆርቋሪ በሆኑ ወጣቶች፣ ምሁራንና ዜጎች የተሞላውን ድርጅት መመሥረታችንበዛሬው እለት ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በይፋ እናበስራልን።
 
ግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል፣ የሕዝብ ሉዓላዊ የሥልጣን ባለቤትነት የተረጋገጠባት፤ የዜጎች መብቶች፣ ሃገራዊ አንድነት፣ ደህንነትና ጥቅም የተከበሩባት ጠንካራና ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ እውን ሆና የማየትን ራዕይ የሰነቀ ድርጅት ነው።
 
የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል ወያኔን በኃይል የማስወገድ፤ ሰላማዊና ዲሞክራሲ የሥልጣን ሽግግር በሃገሪቱ እንዲኖር የማስቻል እና ከማንኛዉም የፓለቲካ ድርጅት ጋር ያልወገኑ ነፃ፣ ጠንካራና ብቃት ያላቸው ህገ-መንግሥታዊ የመከላከያ፣ የፓሊስና የደህንነት ተቋማት እንዲኖሩ አስተዋጽዖ የማድረግ ተልዕኮ ይዞ የተነሳ የኢትዮጵያ ሕዝብ አለኝታ ነው።
 
የግንቦት7 ሕዝባዊ ኃይል ራዕይና ተልዕኮ የተቀዳው በቀጥታ ሕዝብ በህይወቱ በደሙ በስቃይና በመከራ ውድ መስዋዕትነት ከከፈለለት የ1997 ብሄራዊ ምርጫ ነው።

Thursday 20 December 2012

Ethiopia Four Journalists Win Free Speech Prize

 
(New York) - Four Ethiopian journalists have received the prestigious Hellman/Hammett award for 2012 in recognition of their efforts to promote free expression in Ethiopia, one of the world’s most restricted media environments.
 
Eskinder Nega Fenta, an independent journalist and blogger; Reeyot Alemu Gobebo of the disbanded weekly newspaper Feteh; Woubshet Taye Abebe of the now-closed weekly newspaper Awramba Times; and Mesfin Negash of Addis Neger Online were among a diverse group of 41 writers and journalists from 19 countries to receive the award in 2012. Eskinder, Reeyot, and Woubshet are imprisoned in Ethiopia; Mesfin fled in 2009. All four journalists were convicted in 2012 under Ethiopia’s draconian anti-terrorism law.
 
“The four jailed and exiled journalists exemplify the courage and dire situation of independent journalism in Ethiopia today,” said Leslie Lefkow, deputy Africa director at Human Rights Watch. “Their ordeals illustrate the price of speaking freely in a country where free speech is no longer tolerated.”
 
The Hellman/Hammett grants, administered by Human Rights Watch, are awarded annually to writers and journalists around the world who have been targets of political persecution and human rights abuses. The prize is named after two American writers who were harassed during the 1950s anti-communism investigations. Lillian Hellman suffered professionally and had trouble finding work while Dashiell Hammett spent time in prison. A distinguished selection committee awards the grants to honor and support journalists whose work, activities, and lives are suppressed by repressive government action.

Wednesday 19 December 2012

Eskinder Nega Is Currently Appealing His Conviction And Sentencing

Update: Eskinder Nega is currently appealing his conviction and sentencing. On December 19, 2012, the Ethiopian Federal Supreme Court postponed hearing his appeal for the second time. The appeal hearing is scheduled to resume January 18, 2013. Please follow us on Twitter @freedomnoworg for breaking news.
 
Eskinder NegaEskinder Nega, 43, is a prominent Ethiopian journalist who was convicted and sentenced to 18 years in prison on terrorism charges. Prior to his detention, Mr. Nega was a widely published independent journalist and a well-known critic of Prime Minister Meles Zenawi’s government. Mr. Nega is married and the father of one son.
 
Mr. Nega began his work as an independent journalist in 1993 when he founded the Ethiopis newspaper. While Ethiopis and many of the other publications where Mr. Nega later worked were banned, he continued to write articles criticizing the Ethiopian regime’s abuses of power.
 
As a result of his critical reporting, the government has detained Mr. Nega on eight different occasions. In 2005, authorities arrested Mr. Nega and his then-pregnant wife, Serkalem Fasil, who is herself an independent publisher, during a nationwide crackdown following the country’s disputed elections. Mr. Nega was charged with treason and genocide and detained for 17 months before Ethiopia’s High Court released him after a series of negotiations. After releasing Mr. Nega in 2007, the government blocked him from publishing in the country. However, Mr. Nega continued to contribute to online media outlets abroad.

Monday 17 December 2012

Hero Teacher Died Saving Students

 

Out of the chaos and horror emerged an incredible act of selflessness and bravery by one teacher who spent her final moments trying to protect her young students from harm.

Victoria Soto, 27, a first-grade teacher at Sandy Hook Elementary School in Newtown, Conn., ushered her students into a closet, and in so doing placed her body between them and the assailant.

"She was found huddled over her children, her students, doing instinctively what she knew was the right thing," her cousin Jim Wiltsie
tells ABC News.

"I'm just proud that Vicki had the instincts to protect her kids from harm," he continued. "It brings peace to know that Vicki was doing what she loved, protecting the children, and, in our eyes, she's a hero."

Soto was among the six adults, all women, killed in the Friday morning
massacre that also took the lives of 20 children – 12 girls and eight boys. The gunman, identified as 20-year-old Adam Lanza, took his own life. His mother was also found killed in a different location.

Sunday 16 December 2012

ከኢትዮጲያ ብሔራዊ ሽግግር ምክር ቤት የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ

ላለፉት ሀያ አንድ ዓመታት ግፈኛው የህወሃት/ኢሕአዴግ ሥርዓት በአገራችን ኢትዮጵያና ህዝቦችዋ ላይ ያደረሰውን የሰብዓዊ መብት ረገጣ፣ በደልና መከራ ሁሉም የሚያውቀው ነው። በአሁኑ ጊዜ ሥርዓቱ “የመለስን ራዕይ እናሳካለን” በሚል  መፈክር/ፈሊጥ፣  የሰብዓዊ  መብት  ረገጣውን  እና  አምባገነናዊ  አገዛዙን  አጠናክሮ  እንደሚቀጥል  አድማጭ እስኪሰለቸው  ድረስ  እየለፈፈ ይገኛል።  የኢትዮጲያ  ብሔራዊ  ሽግግር  ምክር  ቤት  በቅርቡ  ይህ  ዘረኛ  ሥርዓት በወገኖቻችን ላይ ያደረሰውን በርካታ ግፍና በደል በአገር ውስጥና በውጭ አገር ለሚኖሩ ኢትዮጲያዊያንና ለዓለም ዓቀፉ ሕብረተሰብ በማሳወቅ፣ ድርጊቶቹን አጥብቆ እንደሚያወግዝ ይገልፃል። ባሳለፍናቸው ጥቂት ሳምንታት፤ የህወሃት/ኢሕአዴግ አምባገነናዊ አገዛዝ በወገኖቻችን ላይ ካደረሳቸው በርካታ የሰው ልጅ መብት ረገጣዎች፣ ግፍና በደሎቸ  መካከል የሚከተሉት በዋናናት የሚነሱና በጥብቅ የሚወገዙ ናቸው::

1.  የህወሃት/ኢሕአዴግ  ሥርዓት  በአገራችን  ሕዝብ  ላይ  የሚያደርገው  የሰብዓዊ  መብት  ጥሰት  በግልፅ እንዲወጣ ካደረጉት የቅርብ ጊዜ ክስተቶች መሃል ዓብይ የሚባለው፣ በሙስሊም ሀይማኖት ተከታዮች እምነትና የውስጥ አስተዳደር በሚያደርገው ጣልቃ ገብነት ነው። አክራሪነትን ለመዋጋት በሚል ሰበብ፤ የሀይማኖት  መሪዎች  እንዴት  እንደሚመረጡ  በመወስን፣  ይህንን  የተቃወሙ  አማኞችን  በመደብደብ፤ በማሰርና በመግደል፣ “አኬልዳማ” የሚል አሸባሪ የፈጠራ ፊልም በሚቆጣጠረው ቴሌቪዥን በማሳየት፣ መፍትሔ  ለመፈለግ  የተመረጡትን  ግለሰቦች  በማሰር፣  የፈለጋቸውን  የሀይማኖት  መሪዎች  በቀበሌ
በማስመረጥና  በእስር  የሚገኙትን  የመፍትሔ  አፈላላጊ  ኮሚቴ  አባላትን  ለመጠየቅ  የመጡትን  ሰዎች በማንገላታት ለማስፈራራት መሞከሩ። 

2.  የህወሃት/ኢሕአዴግ ሥርዓት፣ የህሊና እስረኞች በሆኑ ወገኖቻችን ላይ በፈጠራ የአሸባሪነት ክስ የተለያየ  የእስራት  ውሳኔ  ከማስተላለፉ  ባሻገር፤  በሕገ  ወጥነትና  በተለመደ  ዘዴው  ሌሎች ተቃዋሚዋችን ለማስፈራራት የእስክንድር ነጋንና የአንዱአለም አራጌን ንብረት መውረሱ፤ ሥርዓቱ ይቃወመኛል ብሎ የሚያምንበትን ግለሰብ ብቻ ሳይሆን ቤተሰቡንም ለመጉዳት፣ በጋራ የተመዘገበን ንብረት መውረሱ ነው።

Saturday 15 December 2012

ተዘጋጅተን ጠብቀን ዕድል ሳትመጣ ብትቀር ይሻላል ፡፡

ድህነት ባደቀቃት የሚያሚ ቀዬ የተወለደው ሌስ ብራውን በወላጆቹ ስር ለማደግ አልታደለም፡፡ እሱ ብቻ ሳይሆን መንትያ ወንድሙም ከህፃንነቱ ጀምሮ ወላጆቹን አያውቃቸውም፡፡ ሁለቱም በጉዲፈቻ እናታቸው በማሚ ብራውን እንክብካቤ ነው ያደጉት፡፡ ሌስ ቀዥቃዣና ያለ ዕረፍት የሚለፈልፍ ቀባጣሪ ስለነበር ትምህርት የመቀበል ችግር ያለባቸው ልጆች በሚማሩበት ልዩ ት/ቤት ነበር ትምህርቱን የተከታተለው፡፡ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ያጠናቀቀውም በዚያው ት/ቤት ነበር፡፡ ከዚያም የሚያሚ ቢች ከተማ የፅዳት ሠራተኛ ሆኖ ተቀጠረ፡፡ የእሱ ህልም ግን ዲጄ መሆን ነበር፡፡ 
  
ማታ ማታ በባትሪ ድንጋይ የሚሰራውን የቤተሰቡን ሬዲዮ ይዞ ወደ አልጋው በመሄድ፣ ከአካባቢው ሬዲዮ ጣቢያ የሚሰራጨውን የዲጄዎች ወሬና ሙዚቃ ያደምጣል፡፡ የወለል ፕላስቲክ ምንጣፉ በተቀደደው ጠባብ ክፍሉ ውስጥ ምናባዊ የሬዲዮ ጣቢያ በመፍጠር፣ የፀጉር ብሩሽ እንደማይክራፎን እየተጠቀመ ዲጄነትን ይለማመዳል - አዳዲስ የወጡ የዘፈን አልበሞችን በህይወት ለሌሉ (ጐስት) አድማጮቹ እያስተዋወቀ፡፡ አሳዳጊ እናቱና ወንድሙ በስሷ ግድግዳ በኩል ስለሚሰሙት “መለፍለፉን ትተህ አርፈህ ተኛ!” እያሉም ይጮሁበት ነበር፡፡ ሌስ ግን ፈፅሞ አይሰማቸውም፡፡ በራሱ አለም ተመስጦ የራሱን ህልም ይኖራል፡፡

አንድ ቀን የከተማውን ሳር አጭዶ ሲያበቃ፣ በምሳ የእረፍት ሰዓቱ በድፍረት ተነስቶ ወደ አካባቢው የሬዲዮ ጣቢያ ይሄዳል፡፡ የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ቢሮም ይገባና ዲጄ ለመሆን እንደሚፈልግ ይነግረዋል፡፡ ሥራ አስኪያጁ ቁሽሽ ያለ ቱታ የለበሰውንና ኬሻ ባርኔጣ ያጠለቀውን ወጣት ትክ ብሎ እየተመለከተው “ከዚህ በፊት በሬዲዮ ስርጭት ላይ ሰርተሃል?” ሲል ይጠይቀዋል፡፡
ሌስም “በፍፁም ጌታዬ! አልሰራሁም” በማለት ይመልሳል፡፡

Friday 14 December 2012

ህይወቴ አበበ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች

አዲስ አበባ  ታህሳስ 5 2005 ወጣት አርቲስት ህይወቴ አበበ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች። ባለትዳርና የአንዲት ሴት ልጅ እናት የነበረችው አርቲስት ህይወቴ ፥ ታማ በጳውሎስ ሆስፒታል በህክምና ስትረዳ ቆይታ ነው በተወለደች በ31 ዓመቷ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየችው። አርቲስቷ የመቃብር ቁልፎችንና የሰርጉ ዋዜማን ጨምሮ በተለያዩ የመድረክ ቲያትሮች ላይ ሰርታለች። ባለታክሲው፣ ባለቀለም ህልሞችና ሰውዬው ፊልሞች ላይም የሰራች ሲሆን ፥ በርካታ የሬዲዮና የቴሌቪዥን ድራማዎች ላይም በመሪ ተዋናይነት ጭምር መስራቷን ነው የባልደረባችን ዘካሪያስ ብርሃኑ ዘገባ የሚያመለክተው። ካለፉት ሶስት ወራት በፊት ጀምሮ ኑሮዋን በኡጋንዳ ካምፓላ አድርጋ የነበረችው አርቲስት ህይወቴ የቀብር ስነ ስርዓት ነገ በአዳማ ከተማ ይፈጸማል።
 
 

Thursday 13 December 2012

ኢትዮጵያ ቤተእስራኤላዉያን


የኢትዮጵያ ቤተእስራኤላዉያን ሴቶች የዛሬ ስምንት ዓመት ወደእስራኤል ከመሄራቸዉ አስቀድሞ የወሊድ መቆጣጠሪያ በግዳጅ ተሰጥቶናል ሲሉ ማመልከታቸዉን ሰሞኑን የእስራኤል የመገናኛ ብዙሃን ይፋ አድርገዋል።  The Time of Israel የተሰኘዉ ድረገፅ እንዳመለከተዉ ጉዳዩን በአንድ የእስራኤል የቴሌቪዥን ጣቢያ ያብራሩት ኢትዮ-ቤተእስራኤላዉያን ወደእስራኤል ለመሄድ ዴፖ ፕሮቬራ የተባለ የወሊድ መቆጣጠሪያ መድሃኒት በመርፌ ተሰጥቷቸዋል። ዘገባዉ ባለፉት አስርት ዓመታት 50 ሺህ ኢትዮጵያዉያን አይሁዶች ወደእስራኤል መግባታቸዉን ጠቅሶ፤ ለወትሮ ብዙ ልጅ መዉለድ የሚወደዉ ይህ ማኅበረሰብ በአማካኝ የወሊድ ቁጥሩ 50 በመቶ ቀንሶ መታየቱን አመልክቷል።
 
DW AMHARIC NEWS
 

Tuesday 11 December 2012

ተቋርጦ የነበረውና በፍትህ ጋዜጣ አዘጋጅ ላይ የተመሰረተው ክስ ዳግም ተንቀሳቀሰ

አዲስ አበባ ታህሳስ 2  2005 ተቋርጦ የነበረውና በፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ተመስገን ደሳለኝና በጋዜጣው አሳታሚ ማስተዋል የህትመትና ማስታወቂያ ድርጅት ላይ በመገፋፋትና ግዙፍ ያልሆነ የማሰናዳት ተግባር ወንጀል የተመሰረተው ክስ ተንቀሳቀሰ
በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 16ኛ ወንጀል ችሎት ዛሬ ጉዳያቸው የታየው   የፌደራሉ አቃቢ ህግ በ11 ሶስተኛ ወር 2005 ላይ ክሱ እንዲንቀሳቀስ ያቀረበውን አቤቱታ ተቀብሎ ነው ።
የተከሳሽ ጠበቆች ከችሎቱ 2ኛ ተከሳሽ ባለመቅረቡ ድርጅቱን ወክላችሁ ምላሽ መስጠት ትችላላችሁ? ወይ ተብለው ተጠይቀውም እንደማይመለከታቸው ለፍርድ ቤቱ ተናግረዋል ።
 
ጠበቆቹ ምንም እንኳ አቃቢ ህግ ክስ የመመስረት ፣ የማቋረጥና መልሶ የማንቀሳቀስ ሰልጣን እንዳለው በህግ ቢደነገግም አሁን እንዲንቀሳቀስ የተደረገበት አካሄድ ግን ግልፅ አይደለም ብለዋል ።

አቃቢ ህግ በበኩሉ በቂ ተያያዥ ማስረጃዎችን አደራጅቶ የፍርድ ሂደቱ እንዲቀጥል በማሰብ ክሱን ማቋረጡን ያስረዳ ሲሆን የተለያዩ የህግ አንቀፆችን በማጣቀስ ይርጋ እስካላገደው ድረስ በፈለገበት ሰዓት ክሱን ማንቀሳቀስ እንደሚችል ገልጿል ።

ፍርድ ቤቱ ተከሳሹ ከዚህ በፊት ክሱ ተቋርጦ በነበረበት ወቅት በምን ሁኔታ ላይ ይገኝ እንደነበር እንዲሁም የዋስትና ሁኔታውንም ግልፅ በሆነ ሁኔታ እንዲያስረዳ አቃቢ ህግን ጠይቋል ።

አቃቢ ህግ ክሱ ከተቋረጠ በኋላ ተከሳሹ ግለሰብ ከማረሚያ ቤት በዋስ መውጣታቸውን በማስታወስ ለአሁኑ ጉዳይ ተመጣጣኝ ዋስትና በድጋሚ በማቅረብ ውጭ ሆነው ቢከታተሉ ቅሬታ እንደሌለው አስረድቷል።
በዚሁ መሰረት ችሎቱ ግራ ቀኙን መርምሮ ተከሳሽ ተመስገን ደሳለኝ የ50 ሺህ ብር ዋስ ወይም 50 ሺህ ብር በማስያዝ የዋሰትና መብታቸው እንዲከበር በማዘዝ ፥ ሁለተኛ ተከሳሽ ማስተዋል የህትመትና ማስታወቂያ ድርጅት ለጥር 24 2005 ዓመተ ምህረት መጥሪያ ደርሶት እንዲቀርብ በድጋሚ ታዞል።

Ethiopian Women Claim Joint Distribution Committee And Israel Health Ministry Forced Them To Receive Sterilization Shots

Falash Mura women who immigrated to Israel from Ethiopia eight years ago reportedly told Israel Educational Television’s investigative show Vacuum yesterday that they were forced to receive injections of Depo-Provera, the long-lasting birth control drug, as a condition to allowing their immigration.

The women claimed that Israeli representatives from the Joint Distribution Committee (JDC) and the Health Ministry coerced them by telling them that raising large families in Israel is very difficult, that if you have many children it is hard to find work to support them, and that landlords frequently refuse to rent apartments to large families.

50,000 Ethiopian Jews have immigrated to Israel during the past 10 years. During that time, their birthrate reportedly fell by nearly 50 percent.

The women said they were told they had to take what they thought were vaccinations if they wanted to continue to receive medical care from the JDC and be allowed to immigrate.

Many continued to be given Depo-Provera shots once in Israel despite suffering side effects that included severe headaches and abdominal pains.

One woman with osteoporosis told Vacuum that she has been getting Depo-Provera shots for four years without ever being warned by doctors that Depo-Provera is dangerous for women suffering from it.

A hidden camera in an Israeli health clinic filmed an Ethiopian woman being told by a nurse that this shot is usually given only to Ethiopian women.

“[It’s given] primarily to Ethiopian women,” the nurse said, “because they forget, they don’t understand, and it’s hard to explain to them, so it’s best that they receive a shot once every three months…basically they don’t understand anything.”

The Israeli government denied all of the women’s allegations.

However, Vaccum showed a letter from the Health Ministry to Dr. Rick Hodes, the director of the JDC Medical Programs in Ethiopia. The letter praised the Hodes’ work, noting that while fewer than 5% of Ethiopians use any form of birth control, the rate among Hodes’ patients was 30%.

Rachel Mangoli, the director of the WIZO branch in Pardes Hanna, told Vaccum that in 2006 she started a program for Ethiopian children at her local absorption center. A “warning light” lit up when she realized that no babies were born to the center’s Ethiopian residents that year. She checked with the director of the local health clinic and says she was told that all the Ethiopian women at her absorption center had been given contraceptive shots because they could not be relied on to take birth control pills.

In response to Vaccum’s report, the JDC reportedly called the women’s claims “nonsense.”

“The medical team does not intervene directly or indirectly in economic aid and the Joint is not involved in the aliyah procedures,” the JDC statement noted, claiming that Depo-Provera shots are given to Ethiopian women because the JDC’s studies show that it “is the most popular form of birth control among women in Ethiopia.”
 
 Source ( HAARETZ)
 
 

Monday 10 December 2012

የተከበሩ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ

 የተከበሩ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ በውቅታዊ ጉዳዮች ላለፉት ዓመታት አገራዊ ፋይዳ ያላቸውንና ለህዝባችን ሁለንተናዊ ነጻነት የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን በመደገፍ የሚንቀሳቀስው የDemocratic Change in Ethiopia Support Organization Norway des. 9.2012 ባደረጉላቸው የክብር እራት ግብዣ  ከደጋፌዎቻቸው ጋር ተገናኝተው በውቅታዊ ጉዳዮች ውይይት አድርገውል::

 

Saturday 8 December 2012

“ሰው ለሰው” ድራማ በውዝግብ እየተናጠ ነው

ላለፉት ሁለት ዓመታት በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በየሳምንቱ ዘወትር ረቡእ ሲተላለፍ የቆየው “ሰው ለሰው” ተከታታይ ድራማ በፕሮዱዩሰሮች መካከል በተፈጠረ ግጭት ሊታገድ እንደሚችል ምንጮች ጠቆሙ፡፡ በድራማው ላይ የኢንስፔክተር ፍሬዘር እህት ናርዶስን ሆና የምትጫወተው ብስራት ገመቹ፤ ስሰራ የቆየሁት ገፀ - ባህሪ ለእኔ ሳይነገረኝ ለሌላ ተዋናይ መሰጠቱ አግባብ አይደለም ያለች ሲሆን በድራማው ላይ የባለቤትነት ድርሻ ቢኖራትም ሸሪኮቿ ያለእሷ እውቅና ያሻቸውን እያደረጉ መሆኑን ጠቁማ መብቷን ለማስከበር ክስ መመስረቷን ለአዲስ አድማስ ገልፃለች፡፡ ከድራማው ደራሲ የቀረበልኝን የፍቅር ጥያቄ ባለመቀበሌ ጫና ደርሶብኛል ብላለች - አርቲስት ብስራት፡፡
 
የዛሬ ሁለት አመት ድራማው ሊሰራ ሲታሰብ ዳንኤል ሃይሉ፣ መስፍን ጌታቸው፣ ሠለሞን አለሙ እና ነብዩ ተካልኝ በሙያቸው፣ እሷ ደግሞ የገንዘብ መዋጮ በማድረግ በሽርክና ለመስራት መፈራረማቸውን ትናገራለች፡፡
 
ከድራማው ከሚገኘው ገቢ 16.5 በመቶ ድርሻ ስላላትም ለሁለት አመት ስትሰራበት ለቆየችው ትወና ገንዘብ እንዳልተከፈላት እንዲሁም መኖሪያ ቤቷን የድራማው ዋና ገፀባህሪያት መስፍንና ማህሌት መኖርያ ቤት በማድረግ ለቀረፃ ሲያገለግል መቆየቱን ትናገራለች፡፡ በመኖሪያ ቤቷ ቀረፃ ሲከናወን ከስነምግባር ያፈነገጡ ድርጊቶች ስለነበሩ የአምስት ዓመት ልጇን ላለማሳቀቅ ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ በተደጋጋሚ በደብዳቤና በቃል ጠይቃ በመጨረሻም በኢቴቪ ጣልቃገብነት ችግሩ ለጊዜው መፈታቱን ብስራት ገልፃለች፡፡ ሆኖም በየጊዜው ችግሮች መፈጠራቸው አልቀረም ትላለች፡፡ በድራማው ላይ የምታያቸውን ድክመቶች ስትናገር እንደ ፕሮዱዩሰር ስላላይዋት ሊሰሟት እንዳልፈቀዱ ትናገራለች፡፡ የአስናቀ ቅጥር ነፍሰ ገዳይ ሆኖ ይጫወት የነበረው አርቲስት እንደተቀየረ፣ እሴተ ሆና የምትሠራውና የአስናቀ ሚስትም ለረጅም ጊዜ በድራማው እንዳትታይ መደረጉን ገልፃ፣ ተመልካቹም በሁኔታው ደስተኛ እንዳልሆነ ብትነግራቸውም ለማሻሻል ፈቃደኛ እንዳልሆኑ ገልፃለች፡፡
በተለያዩ ጊዜያት ከደራሲው ማስጠንቀቂያ ደብዳቤዎች እንደተፃፈላት የምትገልፀው ብስራት፤ “ለቀረፃ ቤትሽን የማትፈቅጂ ከሆነ እርምጃ እንወስዳለን፣ቀረፃ መቀያየሩን ተረድተሽ የማትመጪ ከሆነና ከቀረፃ በፊት ይነገረኝ የሚለውን ግትር አቋምሽን ካልተውሽ አስፈላጊውን እርምጃ እንወስዳለን” የሚሉ ማስፈራርያዎች እንደደረሳት ትናገራለች፡፡ ሆኖም በወቅቱ “መልህቅ” የተሰኘውን ፊልሟን እየሠራች ስለነበር፣ላለመጨቃጨቅ ብላ ነገሩን ችላ እንዳለችው ገልፃለች - ብስራት፡፡ መስፍን ደራሲ በመሆኑ ለአስር ሳምንት አጠፋሻለሁ ብሎ ከድራማው ውስጥ እንዳጠፋት የምትገልፀው ተዋናይዋ፤ በየጊዜው የሚናገረውን ነገር ሁሉ እንደሚፈፅምባት ጠቁማለች፡፡ ቤቷን ለቀረፃ ፈቅዳ እንደነበር የምትናገረው ብስራት፤ ነገር ግን መስፍን በሚያሳየው የስነምግባር ጉድለት የተነሳ ቤት እንዲቀይሩ ብትጠይቅም፣ኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ለሦስት ወር ብቻ እንድትታገስ፣መስፍንም ከድርጊቱ እንዲቆጠብ ተነግሮት እንደነበር ታስታውሳለች፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ እሷ በማታውቀው ሁኔታ የድራማዋ ናርዶስ በሌላ ተዋናይ (ሜሮን ተሾመ) መቀየሯን ቤቷ ቁጭ ብላ ድራማውን ስትከታተል ማየቷን ገልፃለች፡፡
በድራማው ላይ የሚተውኑ አርቲስቶችን በተለያየ ጊዜ ለመቀየር ፍላጎት እንደነበራቸው፣ ሆኖም ህዝቡ አይቀበለውም በሚል መቅረቱን የተናገረችው ብስራት፤ የ“ሰው ለሰው” ተዋናዮች ሽልማት ይሰጣቸው የሚል ሃሳብ ቀርቦም “ይጠግቡብናል” በሚል መቅረቱን ትናገራለች፡፡
የድራማው ሁለተኛ ክፍል ከተጀመረ አንስቶ ምንም አይነት ክፍያ እንዳልተከፈላት የገለፀችው ብስራት፤ በፊት በየሦስት ወሩ ክፍያ ይከፋፈሉ እንደነበር፣አሁን በየወሩ እንደሆነ ጠቁማ ሆኖም ከደራሲውና ከአዘጋጁ በስተቀር ማንም ክፍያ እንዳልትፈፀመለት ተናግራለች፡፡ በውላቸው መሠረት ሁሉም ነገር የሚወሰነው በሸሪኮቹ ፊርማ መሆኑን የምትናገረው ተዋናይዋ፤ ያለእሷ እውቅና የበፊቱ ድርጅት ተቀይሮ በሌላ ድርጅት መተካቱን፣ ሳያሳውቋት ድርጅቱ ቢሮ መልቀቁንና ሳይነገራት ሠራተኛ መቀጠሩም ከውላቸው ውጪ እንደሆነ ገልፃለች፡፡ ይሄም ሳያንስ ያለምንም ማስጠንቀቂያ ከትወናው መውጣቷ እንዲሁም በሴትነቷ ለደረሰባት ክብረ ነክ ድርጊት ክስ ለመመስረት ወደ ፍርድ ቤት እንዳመራችና ባላት የባለቤትነት ድርሻም ድራማውን ለማሳገድ ጥያቄ እንደምታነሳ ተናግራለች፡፡
የ“ሰው ለሰው” ደራሲ መስፍን ጌታቸውን ስለጉዳዩ በስልክ ጠይቀነው መልስ ለመስጠት ፈቃደኛ እንዳልሆነ የገለፀልን ሲሆን የድራማው አዘጋጅ ሠለሞን አለሙ በበኩሉ፤ ከተዋናይቱ ጋር ውል የነበረን በፊት እንጂ አሁን አቋርጠናል ብሏል፡፡ ውሉ በምን መልኩ እንደተቋረጠ ግን ለመግለፅ ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል፡፡




Friday 7 December 2012

ቴዎድሮስ የት ገባ?”

መለስ በአንደኛ ደረጃ ት/ቤት ውስጥ ጉብኝት እያደረጉ ነው፡፡ ለተማሪዎች ንግግር ካደረጉ በኋላ “አሁን ጥያቄ ካላችሁ መጠየቅ ትችላላችሁ” አሉ፡፡ ቴዎድሮስ የተባለው  ተማሪ ተነሳና “ሦስት ጥያቄዎች አሉኝ” በማለት ጀመረ፡፡ መለስም እንዲጠይቅ ፈቀዱለት “1ኛ. እንዴት ኢ ህ ዲ ግ 99.9% ምርጫውን ሊያሸንፍ ቻለ  2ኛ. ለምንድነው የፀረ-ሽብርተኝነት ህጉን የህዝቡን የጋዜጠኞችን እና ጋዜጦችን  ሃሳብን በነፃነት የመግለፅን መበት የምትጠቀሙበት? 3ኛ. ህወሃት ለምን በሰላማዊ መንገድ ስልጣኑን አይለቅም?” ይሄኔ ደወል ተደወለና ተማሪዎቹ ለእረፍት ከክፍሉ ወጡ፡፡ ከእረፍት መልስ መለስ “ቅድም ውይይታችን ስለተቋረጠ አዝናለሁ አሁን የፈለጋችሁት ልትጠይቁኝ ትችላላችሁ” አሉ፡፡ ቅድስት የተባለች ትንሽ ልጅ ተነሳችና “አምስት ጥያቄዎች አሉኝ” አለች፡፡ ቀጥይ አሏት ጠ/ሚ፡፡ “1ኛ. እንዴት ኢ ህ ዲ ግ 99.9% ምርጫውን ሊያሸንፍ ቻለ? 2ኛ. ለምንድነው የፀረ-ሽብርተኝነት ህጉን የጋዜጠኞችን እና ጋዜጦችን ሃሳብን በነፃነት የመግለፅን መበት ለመገደብ የምትጠቀሙበት?  3ኛ. ህወሃት ለምን በሰላማዊ መንገድ ስልጣኑን አይለቅም?” 4ኛ. ለምን የእረፍት ሰዓት 20 ደቂቃ ቀደም ብሎ ተደወለ? 5ኛ.ቴዎድሮስ የት ገባ?”

Thursday 6 December 2012

Ethiopia: Meles rules from beyond the grave, but for how long?

Rene Lefort  26 November 2012
The trade-off offered by authoritarianism to its client-constituents is security and high growth rates. After Meles challenges may force change, or build the case domestically for a new strong man.
Meles Zenawi, the former Prime Minister of Ethiopia, has been dead for around three months. But the “Melesmania” personality cult, though discreet in his lifetime, shows no sign of fading. From giant portraits in the streets to stickers on the windscreens of almost any vehicle, a smiling Meles is still everywhere.
The sudden death of Meles shook the whole of Ethiopia. The shock quickly gave way to fear of an unknown and threatening future.
The regime did everything to exploit this fear for its own benefit. It has issued continuous calls for the nation to unite around the memory of the dead leader and, above all, around the project he designed and imposed with an iron hand. The new Prime Minister, Hailemariam Selassie, endlessly repeats that he will pursue “Meles’s legacy without any change”. He has replaced not a single cabinet minister. It could be said that the regime is running on autopilot, with the Meles software driving the leadership computer. Plunged into disarray, the governing team is hanging on to this software like a lifebelt. Why?


Wednesday 5 December 2012

Mystery shrouds Ethiopian maid’s death by hanging Egyptian worker falls to death

KUWAIT CITY, Dec 4: An Ethiopian housemaid committed suicide by hanging herself with a rope tied to the ceiling of her room at the sponsor’s residence, reports Al-Nahar daily. Security sources said sponsor of the deceased woman had notified the Operations Room about the incident and Criminal Evidences Men accompanied the rescue team to the scene, but reasons for the suicide remain mysterious, so the remains have since been referred to forensics for autopsy.

Meanwhile, A 33-year-old Egyptian expatriate died when he fell from a building under construction in Mahboula.

Reportedly, when securitymen received information about the accident, they rushed to the location with paramedics and discovered he had succumbed to serious injuries. They referred the corpse to Forensics Department. A case was registered.

In another incident, a Sri Lankan lodged a complaint at Taima Police Station against two unidentified persons he accused of stealing his wallet which contained KD 25 and his civil ID, reports Al-Shahid daily.

According to the complainant, he was walking in an undisclosed location when the suspects blocked his way, threatened to hurt him and took his wallet by force. He provided police with a detailed description of the thieves.

Monday 3 December 2012

አወቃቀሩ የህወሐትን የሥልጣን የበላይነት የሚያስጠብቅ ነው

ጠ/ሚ ሃይለማርያም ደሳለኝ ለምክር ቤቱ አቅርበው ያፀደቁትን አዲስ የካቢኔ አደረጃጀት እንዴት ያዩታል?  ከዚህ በፊት ሰምቼ ነበር፤ ሶስት ቦታ እንክፈለው የሚለውን፡፡ በዛን ጊዜ ግን ስምምነት ላይ አልተደረሰም፡፡ በአንድ ነገር ላይ ግን ስምምነት ላይ ተደርሶ ነበር፡፡ አዲስ የሚመጣው ጠ/ሚኒስትር ማንም ይሁን ማን ከዚህ በፊት የነበረው ጠ/ሚ የነበረውን ሃይል ክምችት ይዞ መቀጠል እንደማይችል ተነጋግረው ጨርሰዋል፡፡ ማን ጠ/ሚ ይሆናል የሚለው አይደለም ወሳኙ፤ ህወሓት አካባቢ ማን እየተሾመ ነው የሚል ነው ወሳኙ፡፡ አሁንም ቢሆን ምንም ወዲያና ወዲህ የለኝም፡፡ በእኔ ግምት ሕወሓት አሁንም ቢሆን ስትራቴጂካዊ ቦታ ላይ ተቀምጧል - ጠ/ሚ ለመሆን፡፡ በሁለት መንገድ ነው እየሄዱ ያሉት፡፡ በውጭ ጉዳይም ትክክለኛ የስልጣን ቅብብል ነው የሚባለው ጉዳይ አሁን ጥያቄ ውስጥ የገባ መሰለኝ፡፡

ህወሓት ከያዘው ቁልፍ የሚኒስቴር መ/ቤቶች ስልጣን አኳያ ከሁለት ዓመት ተኩል በኋላ ሊሆን የሚችለውን ለመገመት ስንሞክር አመራሩ እንደ ዱላ ቅብብል ነው የሚባለው ጥያቄ ውስጥ የገባ ይመስለኛል፡፡ ወሳኝ ወሳኝ ቦታዎችን ወስደዋል፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሄዷል፤ እዛው ተመልሶ ቦታው ገብቷል፡፡ ወሳኝ የሚባለው የፋይናንስና ኢኮኖሚው ሄዷል፤ ተመልሶ ቦታው ገብቷል፡፡ ከሁለት ዓመት በፊት የጠ/ሚኒስትርነት ስልጣኑ (ቢሮ) የተጠናከረ ነውና ለሶስት መክፈል አለብን የሚል ሃሳብ ተነስቶ ነበር፡፡በጊዜው ያ ተቀባይነት አላገኘም፡፡ የጠ/ሚ ቦታ ከህወሓት እጅ ከወጣ የህወሓት የበላይነት ያከትማል የሚል ስጋት ነበራቸው፡፡ አሁን እንግዲህ አንድ ጠ/ሚኒስትርና ሦስት ምክትል ጠ/ሚኒስትሮች አሉን ማለት ነው፡፡ እያንዳንዳቸው ደግሞ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች በክላስተር ተከፋፍለው አስተባባሪነት ተሾሞባቸዋል፡፡

Sunday 2 December 2012

ኢትዮጵያ ሃገራችን  ለዓለማችን በርካታ ምሁሮችን ስታፈልቅ አሁንም እያፈለቀች ያለች ወደፊትም የምታፈልቅ ናት  ግን ለዜጎቹ ባለው ንቀት ዛሬ ደግሞ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽ አስተዳደርን የኃይል ሽያጭ፣ የደንበኞች አገልግሎትና አስተዳደርዊ ጉዳዮችን ለእስራኤሉ ኩባንያ ሰጠ፡፡ ፳ መሐንዲሶች በቅርቡ ወደ አዲስ አበባ መጥተው ሥራውን ይጀምራሉ አለ መንግስት ተብየው

Wednesday 28 November 2012

የብር ምንዛሪ አቅም እየወረደ ነው

በሁለት ዓመት ከ10 በመቶ በላይ ቀንሷል
በዳዊት ታዬ
 
የአንድ ዶላር የምንዛሪ ዋጋ በ17 በመቶ ጨምሮ በ16.35 ብር እንዲመነዘር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መወሰኑ ይፋ ከተደረገበት መስከረም 2003 ዓ.ም. ወዲህ ባሉት ሁለት ዓመታት፣ የብር ምንዛሪ አቅም እየቀነሰ ከ10 በመቶ በላይ መውረዱ ተመለከተ፡፡በኅዳር 2004 ዓ.ም. የየዕለቱ የውጭ ምንዛሪ ዋጋን በሚያመለክተው መረጃ መሠረት የአንድ ዶላር አማካይ የምንዛሪ ዋጋ 17.211 ብር የነበረ ሲሆን፣ በኅዳር 2005 ዓ.ም. ያለው መረጃ የአንድ ዶላር የምንዛሪ ዋጋ ወደ 18.181 ብር ማደጉን ያሳያል፡፡

ከኅዳር 2003 ዓ.ም. እስከ ኅዳር 2004 ዓ.ም. የነበረው የምንዛሪ ዋጋ ከ5.3 በመቶ በላይ ሲጨምር፣ በ2005 በጀት ዓመት የኅዳር ወር የምንዛሪ ዋጋ በአማካይ ወደ 18.181 ብር ማደጉን ተከትሎ ከሌሎች መገበያያ ገንዘቦች አኳያ (በዋናነት ከዶላር) የብር የመግዛት አቅምን በአንድ ዓመት ከ5.56 በመቶ በላይ እንዲወርድ አድርጎታል፡፡ በአጠቃላይ ከኅዳር 2003 ዓ.ም. ወዲህ የብር የመግዛት አቅም በ30 ከመቶ እንዲወድቅ ምክንያት ሆኗል፡፡

ባለፉት ሁለት ዓመታት የታየው የምንዛሪ ለውጥ ግን በመስከረም 2003 ዓ.ም. በብሔራዊ ባንክ በአንዴ ከተደረገው ጭማሪ በተቃራኒው ቀስ በቀስ በየዕለቱ ይካሄድ በነበረው የውጭ ምንዛሪ ግብይት ላይ ተመርኩዞ እየጨመረ የመጣ ነው፡፡ ቀስ በቀስ የታየው ለውጥ በፍጥነት እያደገ የመጣው ደግሞ ካለፈው መጋቢት 2004 ዓ.ም. ወዲህ መሆኑንም መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

ባለፉት ሁለት ዓመታት የታየው የምንዛሪ ለውጥ ብሔራዊ ባንክ የብር ምንዛሪ ለውጥ በአንዴ ከማድረግ ይልቅ፣ ቀስ በቀስ እየጨመረ እንዲሄድ ማድረግ መምረጡን ያሳያል የሚሉ የኢኮኖሚ ባለሙያዎች፣ በሁለት ዓመታት ጊዜ ውስጥ ከ10 በመቶ በላይ የደረሰው ጭማሪ ከፍተኛ እንደሆነም ይገልጻሉ፡፡

የብር ምንዛሪ ለውጡን በአንድ ጊዜ ከመለወጥ ባለፉት ሁለት ዓመታት እንደታየው ቀስ በቀስ እንዲለወጥ ማድረጉ በአንድ በኩል የተወሰነ ጠቀሜታ ቢኖረውም፣ የዋጋ ግሽበት እንዳይወርድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል ይላሉ፡፡

Friday 23 November 2012

“ባልና ሚስት ምንድን ናቸው?”

“ባልና ሚስት ምንድን ናቸው?” በሚል ንዑስ ርዕስ ስር፣ የባልና ሚስትን አካላዊና ስነ ልቦናዊ ጥምረት፣ የመንፈስ አንድነት “ባልና ሚስት አብረውና በደስታ ለመኖር የፈለጉ እንደሆነ እያንዳንዳቸው ሶስት ሶስት መሆን አለባቸው”  “መጀመሪያ ባልየው ሌት ተቀን እንደ ሎሌ ታጥቆ የሚሠራ÷ ለቤቱ የሚያስብ በአዳራሽ ሲገኝ ደግሞ ጌታ መስሎ÷ ተኮፍሶ÷ እንግዳውን የሚቀበል÷ ልጆቹን የሚያዝዝ÷ የቤቱን ሥነ-ሥርዓት የሚቃኝ÷ በመኝታ ቤት ግን ተጫዋች መሆን አለበት” 

 “ምሽት የማድቤት ገረድ÷ የሳሉን እመቤት÷ የመኝታ ቤት እብድ መሆን አለባት እንጂ በጠቅላላው የተኮፋፈሱ እንደሆነ ሦስት ባህሪ ከሌላቸው ባልና ምሸት አይሆኑም” ወሲብንና ስነልቦናዊ ጥምረትን በባለትዳሮች ላይ ያላቸውን ሰፊ ቦታ፣ በቅኔያዊ ጨዋታ በብልሃት ለዘብ አድርገው ያስረዱበት መንገድ በርግጥም የደራሲውን ልዩ ብቃት ያመለከተ ይመስለኛል፡፡ 

የአለማየሁ ሞገስ



Thursday 22 November 2012

ዝኆኑም ትንኙም ዝኆኑም ትንኙም

አንበሳ በሚገዛው አንድ ጫካ ውስጥ አያሌ እንስሳት ይኖሩ ነበር፡፡ አንድ ቀን አንበሳ ለአንድ የሥራ ጉዳይ ወደ ሌላ ሀገር ለመሄድ ተነሣ፡፡ የእርሱ መሄድ በእንስሳቱ ዘንድ በተሰማ ጊዜ የጫካውን ሕልውና በተመለከተ ጥያቄ ተነሣ፡፡ ጦሩን ማን ይመራል? ገንዘብ ማን ይይዛል? ምግብ ማን ያከፋፍላል? መልእክት ማን ይቀበላል? ዳኝነት ማን ይሰጣል? ሠራተኛ ማን ያሠማራል? ሹመት ማን ይሰጣል? እያሉ እንስሳቱ መጠያየቅ ጀመሩ፡፡ በዚያ ጊዜ አንበሳ ሁሉንም ነገር ጠቅልሎ ይዞት ስለነበር አሁን እርሱ ሲሄድ ነገር ዓለሙ ሁሉ ሊዛባ ደረሰ፡፡
አንበሳ ችግሩን ቢረዳውም ነገር ግን ለአንዱ እንስሳ ብቻ ሥልጣኑን ሰጥቶ መሄዱ እስከ ዛሬ ድረስ ከእርሱ በታች እኩል ሆነው የኖሩትን ታማኞቹን ማባላት መስሎ ታየው፡፡ ስለዚህም ‹ሥልጣን በተርታ ሥጋ በገበታ› ብሎ ሥልጣኑን ቆራርሶ ለሁሉም በየዐቅማቸው ለማካፈል ወሰነ፡፡ በዚህም መሠረት ነበርን የጦር ሚኒስትር፣ ዝንጀሮን ዋና ዳኛ፣ ጦጣን የገንዘብ ተቆጣጣሪ፣ ቀበሮን የሥጋ ኃላፊ፣ ዝሆንን ምግብ አከፋፋይ፣ አጋዘንን የሠራተኞች ተቆጣጣሪ፣ ተኩላን ፖሊስ አድርጎ ሰየማቸው፡፡
ሁሉም የጫካው እንስሳት ሹመት ሲደርሳቸው ሁለት እንስሳት ግን ምንም ሳያገኙ ቀሩ፡፡ ኤሊ እና ጥንቸል፡፡ አንበሳውም ‹‹ዔሊ እጅግ ዘገምተኛና ዛሬ ተነሥታ የዛሬ ሳምንት የምትደርስ ፍጡር ናት፡፡ ለእርሷ ሹመት መስጠት ማለት በሹመት ላይ መቀለድ ማለት ነው›› ሲል እንስሳቱ ሁሉ ሳቁ፡፡ ወደ ጥንቸልም ዞር ብሎ ‹አንቺ ሚጢጢ ፍጡር አሁን ላንቺ ሥልጣን ቢሰጥሽ ምን ታደርጊበታለሽ›› ሲል ተሳለቀባት፡፡ ይህም በእንስሳቱ ሳቅ ላይ ሌላ የሳቅ ዳረጎት ጨመረላቸው፡፡
አንበሳውም ወደ ጉዳዩ ሄደ፡፡

Mercy Mercy

Katrine Riis Kjær, Denmark, 2012
At first sight, adoption seems like a win-win situation: a poor orphan gets some loving parents and a good life. But the world of adoption is a question of supply and demand, with Ethiopia as a chief supplier of thousands of needy children. The fact that the well-being of the child is not always top priority becomes painfully clear in this tragic story about Masho and her little brother Roba. Far from being orphans, their sick parents give them up for adoption in the hope they'll have a better life. The two toddlers move to Denmark with their new parents, but are they better off now? For four years, Katrine Kjaer followed both parent couples in their growing sense of hopelessness. Danes Henriette and Gert are on the verge of despair over the rebellious Masho, who doesn't want to adjust to her new family. Ethiopians Sinkenesh and Husen are desperate because they're not receiving any news about their children, as the adoption agency promised. Kjaer records it all. Emotional moments such as the transfer of the children and the tensions in their home in Denmark are shot from a respectful distance. Without losing sight of the nuances, the film shows the downside to international adoption, the contrast between Ethiopia and Denmark, and the parallel pain of both parents and children.

Wednesday 21 November 2012

"የኢትዮጵያ ዘመናዊ የህፃናት የውጭ ንግድ"

ጉዲፈቻ ታሪክ በኢትዮጵያ በባህላዊ መንገድ ሲደረግ የቆየ ነው መቼ እንደተጀመረ በእርግጠኝነት ለማወቅ ባይቻልም በ18 ክፍለ ዘመን በኦሮሞ ብሔረሰብ እንደተጀመረ ይታሰባል። ጉዲፈቻ የሚለው ቃል የመጣው ከኦሮሚኛ ቋንቋ ሲሆን ትርጓሜውም ተፈጥሮዓዊ የወላጅነትና የልጅነት የሥጋ ዝምድና ሳይኖር ከሌላ ሰው አብራክ የተወለደን ልጅ ኢኮኖሚያዊ ማህበራዊ ጥቅሙን ጠብቆ እንደ አብራክ ክፋይ ልጅ ማሳደግ ማለት ነው። በኢትዮጵያ የጉዲፈቻ ሕግ ለመጀመሪያ ጊዜ በ1952 ዓ.ም በወጣው የፍትሐብሔር ሕግ ማዕቀፍ ተሰጥቶታል ይህም ሕግ የሕፃኑን መብት የሚያስጠብቅ ሆኖ የተዘጋጀ ነው።
 
የጉዲፈቻ ዓላማ ከውርስ ሥርዓት ጋር በተያያዘ የዘር ሃረግን ለመቀጠል፤ የዝምድና ትስስር ለማጠናከር፤ ፖለቲካዊ ሃይማኖታዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞችን ለማግኝት፤ … ጥቂቶቹ ናቸው። ለምሳሌ በሀገራችንም የተለያዩ ጦርነቶች በጎሳዎች መካከል ሲነሱ የአንዱን ጎሳ ልጅ አንዱ ጉዲፈቻ ያደርጋል በዚህም ሰበብ በጎሳዎቹ መካከል ሰላም ይፈጠራል።
 
በተለያዩ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ቀውሶች ምክንያት የድንበር ተሻጋሪ ጉዲፈቻ እየጨመረ መጥቷል። ሀገሮች ለጉዲፈቻ ልጆች ምንጮች የሚሆኑበት ምክንያት በርካታ ናቸው። በሃገራችን እ. ኤ. አ. በ2004 በተደረገ ጥናት ኢትዮጵያ ከቻይና፣ ጓቲማላ፣ ሩሲያና ሶሪያ ቀጥላ በአምስተኛ ደረጃ የጉዲፈቻ ምንጭ ሀገር ለመሆን መብቃቷ ታውቋል። እ. ኤ. አ. በ2006 ላይ የተለያዩ ሀገሮች እየቀነሱ በመምጣታቸው ኢትዮጵያ አራተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች። እ. ኤ. አ. በ2010 ደግሞ አብዛኞቹ ሃገሮች በከፍተኛ ደረጃ በመቀነሳቸው ኢትዮጵያ ሁለተኛ ሆናለች።

Tuesday 20 November 2012

Uenige om når et barn er norsk








Hvor lenge må et asylbarn være i Norge for være norsk nok for å få oppholdstillatelse? En splittet regjering behandlet tirsdag dette spørsmålet i Stortinget.
20. november 2012 kl. 20.58, oppdatert 20. november 2012 kl. 22.12 |kommentarer |

Stortinget debatterte regjeringens stortingsmelding «Barn på flukt», hvor regjeringen og Arbeiderpartiet nekter å sette en tidsgrense for å sikre at asylbarn skal få opphold.
– Det kommer vi ikke til å sette noe absolutt grense på. Det viktigste argumentet mot, er jo at en absolutt grense kanskje vil friste en del til å prøve å hale ut tiden, sier saksordfører i Arbeiderpartiet Lise Christoffersen.

Ønsker en avklaring i Høyesterett

Advokat Håkon Bodahl-Johansen. (Foto: Anne Lognvik/NRK)Advokaten til Verona Delic, Håkon Bodahl-Johansen, la fram detaljer for bakgrunnen for saken, i retten i dag.
Foto: Anne Lognvik/NRK
I dag startet Høyesterett behandlingen av saken til Verona Delic som sammen med familien er utvist fra Norge til Bosnia.

Sunday 18 November 2012

የሰማዕታት ቀን በኦስሎ

የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በዛሬው ዕለት በኦስሎ በዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት አዘጋጅነት ለወጣቱ ስለፍትህ ስለ ነፃነት ስለ ሰብአዊ መበት መከበር ሲል ውድ ህይወቱን ቤዛ ላደረገልን መምህር የኔሰው ገብሬ እና በግፍ ለታሰሩት ለተገደሉት የነፃነት ታጋዮች የሻማ ማብራት ስነ ስርዓት ተካሄዶል በዚሁ ስነ ስርዓት ላይ ዶ/ር ሙሉ ዓለም ባደረጉት ንግግር በውጭ ሀገር የምንኖር ኢትዮጵያውን  ከምንጊዜውም በበለጠ ህብረትና ወገናዊ ፍቅርን በመካከላችን በመመስረት በህዝባችን ላይ እየደረሰ ያለውን የሰብዓዊ መብት እረገጣ ሰለቸኝ ደከመን ሳንል ለህዝባችን ነፃ መውጣት መታገል አለብን ሲሉ ተናግረዋል በዝግጅቱ ላይ  የመታሰቢያ ግጥሞች ንግግሮች ተደርገዋል።
 
Nov.18.11.12

Saturday 17 November 2012

Norway refuses to grant Ethiopia’s fingerprint request of over 400 refugees

Saturday, 17 November 2012 06:48 
By MERGA YONAS 
 
The Norwegian government has disagreed with Ethiopia on the latter's request for fingerprints of the over 400 Ethiopian refugees residing in Norway, who were expected to be deported, as it is not in their repatriation agreement. On January 26, Torgeir Larsen, Secretary of state with Norwegian government and Ambassador Berhane Gebrekristos, Minister of Foreign Affairs, signed a Memorandum of Understanding to repatriate back Ethiopian citizens in Norway. Since March 15, the Norwegian government was in the process of sending back over 400 Ethiopian refugees living in the country without legal documents or resident permits.

Sources told the The Reporter that though the Ethiopian government requested as a precondition fingerprints of the Ethiopians who are set to be deported, the Norwegian government refused to get engaged as the request was not in their repatriation agreement.

The agreement was signed between the two countries to let citizens repatriate voluntarily, Ambassador Dina Mufti, spokesperson with the Ministry of Foreign Affairs told The Reporter. According to the agreement, the repatriation is going to be carred out by the Norwegian government.

“Thus, we don’t follow up the status and I don’t have any information regarding the fingerprint request,” Dina told The Reporter.

“In the first place there was no one who could voluntarily return back to Ethiopia, as many are political refuges and that is why the demonstration has kept on here in Norway,” an Ethiopian who resides in Norway told The Reporter in a telephone interview.

Wednesday 14 November 2012

ፍርደኛው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እንዲወረስ ጥያቄ በቀረበበት ንብረቱ ጉዳይ አልከራከርም አለ

አቶ አንዱዓለም አራጌም ፍርድ ቤት ቀርበዋል
በታምሩ ጽጌ

በዚህም ምክንያት ወደ ፍርድ ቤት ከዛሬ በኋላ እንዳልቀርብ ለማረሚያ ቤት ትዕዛዝ ይሰጥልኝ፤” በማለት አመልክቷል፡፡
 
በሽብርተኝነት ወንጀል ተከሶ በ18 ዓመታት ፅኑ እሥራት እንዲቀጣ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሦስተኛ ወንጀል ችሎት ውሳኔ ያሳረፈበት ፍርደኛው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ ዓቃቤ ሕግ እንዲወረስ ስለጠየቀበት የንብረት ጉዳይ ቤተሰቡም ሆነ እሱ መከራከር እንደማይፈልጉ ለፍርድ ቤቱ አስታወቀ፡፡ በነሐሴ ወር 2004 ዓ.ም. የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ በሽብርተኝነት አዋጁ በተቀመጠው አንቀጽ መሠረት፣ “በሽብር ወንጀል የተቀጣ ግለሰብ ንብረት መወረስ እንዳለበት ያዛል” በሚል ለፍርድ ቤት ባቀረበው ጥያቄ መሠረት፣ ንብረታቸው እንዲወረስ ከተጠየቀባቸው ፍርደኞች መካከል በዕድሜ ልክ ፅኑ እሥራት እንዲቀጣ የተወሰነበት አንዱዓለም አራጌና ጋዜጠኛ እስክንድር ትናንትና ፍርድ ቤት ቀርበው ነበር፡፡

በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አራተኛ የወንጀል ችሎት ቀርበው የነበሩት የአንድነት ፓርቲ አመራር አቶ አንዱዓለም አራጌና ባለቤታቸው ዶክተር ሰላም አስቻለው፣ እንዲወረስባቸው የተጠየቀውን አንድ የቤት መኪና በሚመለከት ተቃውሞ እንዳላቸው ለፍርድ ቤቱ በጽሑፍ አቅርበዋል፡፡

ሌላው ዓቃቤ ሕግ ንብረቱ እንዲወረስ ለፍርድ ቤት ጥያቄ ያቀረበበት፣ በሌለበት ጥፋተኛ ተብሎ በ15 ዓመታት ፅኑ እሥራት እንዲቀጣ የተወሰነበትና ኑሮውን በአሜሪካ ያደረገው አበበ በለው ሲሆን፣ ባለድርሻ ይሆናሉ ያላቸውን የባለቤቱ አድራሻ ማግኘት አለመቻሉን ለፍርድ ቤቱ አስታውቋል፡፡ በመሆኑም ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ እንዲሰጥበት አመልክቷል፡፡

በመቀጠል ጋዜጠኛ እስክንድር ከተቀመጠበት የተከሳሾች መቀመጫ ሳጥን ውስጥ ቆሞ የሚያቀርበው ሐሳብ እንዳለው በመግለጽ፣ “እኔም ሆንኩ ባለቤቴ በንብረት ውርስ ምክንያት መከራከር አንፈልግም፡፡ በዚህም ምክንያት ወደ ፍርድ ቤት ከዛሬ በኋላ እንዳልቀርብ ለማረሚያ ቤት ትዕዛዝ ይሰጥልኝ፤” በማለት አመልክቷል፡፡

Thursday 8 November 2012

ፀሎት

ልዑል እግዚአብሔር ሆይ ሃገሪን
በታማኝነት በቅንነት እንዳገለግል እርዳኝ
ልዑል እግዚአብሔር ሆይ ሃገሪን በታማኝነት በቅንነት እንዳገለግል እርዳኝ





Wednesday 7 November 2012

ዋይ ዋይ ሲሉ የርሃብን ጉንፍን ሲስሉ


ሕፃናት አካላዊ ማህበራዊና ስነ ልቦናዊ ጉዳት ከሚያደርሱ ነገሮች ሁሉ መጠበቅ አለባችው ሀገራችን ህፃናቱ ትምህርት ቤት ሲሄዱ የሚላስ የሚቀመስ በቤታችው ጠፍቶ ጠኔ አዙሮ እየደፍችው ነው የኢትዮዽያ መንግስት ተብየው  ኮምፒውተርን እንደምግብ አቅርቦላቸዋል





 

Why I hope kids in Ethiopia can teach the rest of us something profound about education.


                    Self-taught: Children in Ethiopia are learning to use tablets distributed by OLPC.
 
Seymour Papert, a computer scientist and pioneer in artificial intelligence, once said: “You cannot think about thinking unless you think about thinking about something.” Does this apply to learning? Maybe not.

Here is what I mean.

Stakkars Etiopiske Barn !!!

Et eksperimentet fant sted i noen utvalgte avsidesliggende landsbyer i Etiopia. Barna fikk utdelt små datamaskiner av typen Motorola Xooms, skriver publikasjonen MIT Technology Review.
Disse observasjoner villle være interessante om forfatteren snakket om ville aper og ikke om mennesker. Stakkars Etiopiske barn !!!
             
 
Leder:"Etiopiske barn fikk PC-er, begynte å utdanne seg selv"
 
Maskinene, såkalte tablets, var fra før utstyrt med flere undervisningsapplikasjoner, og batteriene ble ladet ved hjelp av solcellepaneler. Men de ble levert i lukket emballasje, uten noen instrukser for hvordan de skulle betjenes.
Forskerne trodde barna, som knapt hadde sett noen skrevne ord tidligere, ville være uforstående til datahjelpemidlene. Men etter bare fire minutter hadde ett av barna åpnet boksen og slått på datamaskinen.

Monday 5 November 2012

አልሠለጥን ያለው የዳያስፖራ ፖለቲካ

ዳዊት (እውነተኛ ስሙ እንዲገለጽ አይፈልግም) በኖርዌይ ለአምስት ዓመታት ያህል ቆይታ አድርጓል፡፡ በአሁኑ ወቅት ቤተሰቡን እዚያ ትቶ ኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ ሥራዎች የተሰማራ ወጣት ነው፡፡ በተሰማራበት ሥራም ውጤታማ ሳይሆን አይቀርም ደስተኛ ነው፤ ቤተሰቡን ለማምጣት ካልሆነ በስተቀር ተመልሶ እዚያ አገር የመኖር ፍላጎት የለውም፡፡ በኖርዌይ ውስጥ በነበረው ቆይታ ብዙም መልካም ትውስታ ያለው አይመስልም፡፡

ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ የግል ባንኮች መካከል ስሙ ከሚጠቀስ አንድ ታዋቂ ባንክ የቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ ሆኖ በቂ የሚባል ደመወዝ እየተከፈለውና መኪና ተመድቦለት፣ እንዲሁም የተለያዩ ጥቅማ ጥቅሞች እያገኘ መልካም የሚባል ኑሮ የሚኖር ሰው፣ በሥራ ምክንያት ወደ ኖርዌይ አቅንቶ እዚያው ስለመቅረቱ ዳዊት አውግቶናል፡፡

‹‹ዛሬ ነገ እየተባለ የፖለቲካ ጥገኝነቱ ምላሽ አግኝቶ እዚያው አገር የተሻለ ሥራ ሠርቶ ለመኖር የነበረው ምኞት ሳይሳካ የባንኩ ሰው ይኼው ሁለት ዓመት ሞልቶታል፤›› ይላል ያንን የመቅረት ዕርምጃ የወሰነበትን ቀን እየረገመ እንደሚኖር እያስታወሰ፡፡ በርካታ ኢትዮጵያውን ምንም የፖለቲካ ዕውቀትና ፍላጎት ሳይኖራቸው እዚያ አገር የመኖርያ ፈቃድ አግኝተው ለመኖርና ሕይወታቸውን ለመቀየር ሲሉ፣ ላቀረቡት የፖለቲካ ጥገኝነት ጥያቄ ምላሽ ሲጠባበቁ እየተሰቃዩ ይኖራሉ ይላል፡፡

Sunday 4 November 2012

ኢትዮጵያችንን እየሰጠናት ወይስ እየነጠቅናት?!

‹‹አገሬ ለእኔ ምን አደረገችልኝ ብለህ ከመጠየቅህ በፊት እኔ ለአገሬ ምን አደረግኩላት ብለህ ጠይቅ›› ብለው ነበር የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ጆን ኤፍ ኬኔዲ፡፡
 
እኛም ደግመን ደጋግመን እንለዋለን፡፡ ‹‹ላድርግላት›› የሚል እየጠፋ ‹‹ታድርግልኝ›› የሚል እየበዛ ነውና፡፡ ‹‹የሰጪ›› ቁጥር እያነሰ ‹‹የነጣቂ›› ቁጥር እየበዛ ነውና፡፡

እስቲ እንደ መንግሥትም፣ እንደ ሕዝብም፣ እንደ ግለሰብም፣ እንደ ዜጋም ራሳችንን እንፈትሽ፡፡ የድርሻችንን እየተወጣን ነን? እስቲ መንግሥትን ከመፈተሻችን በፊት እንደ ሕዝብና እንደ ዜጋ ራሳችንን እንፈትሽ፡፡

ኢትዮጵያችን ከጉቦ፣ ከሙስናና ከአድልዎ ፀድታ ሕገ መንግሥቱን መሠረት አድርጋ የምትንቀሳቀስ አገር እንድትሆን እንመኛለን፡፡ ነገር ግን ራሳችን እነዚህን እኩይ ተግባራት እንታገላለን? ጉቦ ሰጪ ከሌለ ጉቦ ተቀባይ እንደማይኖር አውቀን እምቢ አንሰጥም ብለን በፅናት እንቆማለን? ጉቦ የሚሰጡትንና ጉቦ የሚቀበሉትን እናጋልጣለን? ፈርተን ወይም እኛም ጉዳያችን እንዲፈጸምልን ብለን ተባባሪ እንሆናለን?

እዚህ ላይ ከፍተኛ ጉድለትና ድክመት በዜጎችና በተለይም እንደ ሕዝብ እየታየብን ነው፡፡ ጠንክረን ሙስናን እየታገልን አይደለም፡፡ አገራችን ስትነጠቅ፣ ስትሰረቅና በሙስና ስትጨማለቅ የድርሻችን እየተጫወትን አንገኝም፡፡ ሌላው እንዲሠራው እንጂ እኛ ራሳችን ኃላፊነታችንን አንወጣም፡፡ አገራችን እንድትነጠቅ እየተባበርን ነን፡፡ ይህ ሁሉ የሚሆነው ስለማንታገል፣ ለመብታችን ስለማንቆምና ግዴታችንን ስለማንፈጽም ነው፡፡

ወንጀል እንዲጠፋ እንፈልጋለን፡፡ መንግሥት ይህን ለምን አያደርግም፣ ፖሊሶች ለምን ዝም ይላሉ፣ ወንጀልኮ እየበዛ ነው፣ ሌብነት ተስፋፋ እንላለን፡፡ ሌላው ማድረግ ያለበትን አለማድረጉ ያስጠይቀዋል፡፡ ነገር ግን እኛ ራሳችንስ እንደ ዜጋና እንደ ሕዝብ ወንጀል ሲፈጸም ስናይ ምን ያህል እንታገላለን? ራሳችን ምን ያህል እናጋልጣለን? የመንግሥትና የሕዝብ ንብረት በየመንገዱ ሲዘረፍ ስናይ ፈርተን ዝም እንላለን ወይስ ደፍረን እናጋልጣለን? መኪና መንገድ ላይ ሲሰረቅ እያየን ዝም፣ የአገር የኤሌክትሪክ፣ የስልክ፣ የውኃ ቧንቧዎች፣ ሽቦዎችና የተለያዩ ዕቃዎች ሲሰረቁ ዝም እንላለን፡፡

ዜና ዜና ከአሥር ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ከኢትዮጵያ 15 ቢሊዮን ዶላር መውጣቱ ተረጋገጠ

ካቻምና ብቻ 3.5 ቢሊዮን ዶላር ታጥቷል
 
እ.ኤ.አ. ከ2001 እስከ 2010 ባለው ጊዜ ውስጥ 15 ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ገንዘብ ሕጋዊ በሆነና ባልሆነ መንገድ ከኢትዮጵያ እንዲወጣ ተደርጎ ወደ ውጭ ገበያዎች ማምራቱን በቅርቡ ይፋ የሆነ ሪፖርት አመለከተ፡፡ ይህ ችግር በመላ አፍሪካ ትኩረት እየሳበ እንደመጣ ታውቋል፡፡

የፋይናንስ ምንጭ በእጅጉ ከሚያስፈልጉዋቸው ታዳጊ አገሮች ወደ ሌሎች አገሮች ገንዘብን በማዘዋወርና በሕገወጥ የፋይናንስ ግብይት እየወጣ ያለውን ሀብት በተመለከተ እ.ኤ.አ. ከ2009 ጀምሮ ሲወጡ የነበሩ ሪፖርቶች የሚያረጋግጡት፣ ክስተቱ ትኩረት እየሳበ መምጣቱን ነው፡፡ ኢትዮጵያ ያላትን ውስን የውጭ ምንዛሪ መጠን ይኼው ከፍተኛ የካፒታል ማዛወር ወይም ማሸሽ ተግባር በእጅጉ እየታየባት በመምጣቱ፣ የመነጋገርያ አጀንዳ እንድትሆን አድርጓታል፡፡

ተሻሽለው የወጡ አኀዞች እንደሚያመለክቱት፣ እ.ኤ.አ. ከ1970 እስከ 2010 በነበሩት ሰላሳ ዓመታት 24 ቢሊዮን ዶላር ከኢትዮጵያ እንዲሸሽ ተደርጓል፡፡ ገንዘብ በከፍተኛ መጠን እየሸሸ መሆኑ ከተመዘገበባቸው ጊዜያት ትልቁን ድርሻ መያዝ የጀመረው እ.ኤ.አ ከ2000 በኋላ ያለው ሲሆን፣ በተለይ እ.ኤ.አ. በ2010 ብቻ 3.5 ቢሊዮን ዶላር በአገሪቱ ኢንቨስት ያደረጉ የውጭ ባለሀብቶች ያሸሹት ገንዘብ (ካለፈው ዓመት ኅዳር ወር አኳያ ከአገሪቱ የውጭ ምንዛሪ መጠባበቂያ ክምችት በላይ ሆኖ ተመዝግቧል) በከፍተኛነቱ ሲጠቀስ፣ ከዚህ መጠን ቀጥሎ የተመዘገበው ከፍተኛ የገንዘብ ማሸሽ እ.ኤ.አ. በ2002 የታየው የ3.1 ቢሊዮን ዶላር ነው፡፡ በሪፖርቱ የቀረቡት መረጃዎች ሲፈተሹ፣ ባለፉት ሰላሳ ዓመታት ውስጥ ከፍተኛ የካፒታል ማሸሽ የተመዘገበባቸው ጥቂት ዓመታት ሆነው ይገኛሉ፡፡

ካፒታል የማሸሽ መጠኑ እ.ኤ.አ. ከ2001 ጀምሮ በ2.1 ቢሊዮን ዶላር እየተመነደገ መምጣት ሲጀምር፣ 2002፣ 2003፣ 2004፣ 2007፣ 2009 እንዲሁም 2010 ላይ በእያንዳንዱ ዓመት የ1.4 ቢሊዮን ዶላር መጠን የመዘገበበት የገንዘብ መጠን ከአገሪቱ ወጥቷል፡፡

ሪፖርቱ ያካተታቸው ጊዜያት የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን የመጨረሻዎቹ አራት ዓመታት፣ እንዲሁም የደርግን የመጨረሻዎቹ አሥር ዓመታት ሲሆን፣ በእነዚህ ጊዜያት ከተመዘገበው የገንዘብ ማሸሽ በልጦ የተገኘው ግን ባለፉት አሥር ዓመታት የተመዘገበው መጠን ነው፡፡

እ.ኤ.አ. በ1982 ከአገሪቱ የወጣው የገንዘብ መጠን 2.8 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን፣ ይህም ከፍተኛው በመሆን ተመዝግቦ የቆየ መጠን ነበር፡፡ ይህ ቢባልም በ1981 1.5 ቢሊዮን ዶላር፣ በ1985 1.3 ቢሊዮን ዶላር እንዲሁም በ1987 1.9 ቢሊዮን ዶላር በመውጣቱ ይህንን ጊዜ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ከአገሪቱ የሸሸበት ሁለተኛው ዘመን እንዲሆን አስችሎታል፡፡

ከሰሐራ በታች ከሚገኙ አገሮች 33 አገሮች በአጠቃላይ 814 ቢሊዮን ዶላር የሸሸ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 591 ቢሊዮን ዶላሩ በዚሁ ቀጣና ከሚገኙ ነዳጅ አምራች አገሮች እንዲወጣ የተደረገ ነው፡፡ ይህን ያህል መጠን ካፒታል እየሸሸ የሚገኘው ደግሞ የአገሮቹ የነዳጅ ገቢ እያደገ በመጣበት ጊዜ ሆኖ ሲመዘገብ፣ በተለይ ናይጄሪያ 311.4 ቢሊዮን ዶላር የሸሸባት ትልቋ አገር ሆኖ ተገኝታለች፡፡

በሪፖርቱ አስገራሚ የሆነው ሌላው ጉዳይ ደግሞ እየሸሸ የሚገኘው ካፒታል በቀጣናው በይፋ የተሰጠውን 659 ቢሊዮን ዶላር እንዲሁም ከውጭ በቀጥታ ከተገኘው የ306 ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንት በልጦ መገኘቱ ነው፡፡ ይበልጡን አስገራሚ የሆነው ደግሞ ከሰሐራ በታች ያለው አካበቢ ለተቀረው ዓለም አበዳሪ ሆኖ የተገኘበት አጋጣሚ ሲሆን፣ እየሸሸ ከሚገኘው ከፍተኛ ገንዘብ በተፃራሪ የቀጣናው የዕዳ መጠን 189 ቢሊዮን ዶላር ሆኖ በመገኘቱ ነው፡፡

ይህ ሪፖርት ከሌሎች በካፒታል ሽሽት ላይ ከተደረጉ ጥናቶች የተለየ እንዲሆን ካደረጉት ነጥቦች መካከል ያለደረሰኝ የሚካሄዱ የንግድ ልውውጦችን፣ እንዲሁም የሐዋላ ገቢዎች በአገሪቱ ኦፊሴላዊ የሒሳብ መዛግብት ውስጥ ተካተው አለመገኘታቸው የሚያስከትለውን ተፅዕኖ ማካተቱ ነው፡፡

ያለደረሰኝ የሚካሄዱ የወጪና ገቢ ንግድ ጉዳቶች ላኪዎች ሆነ ብለው ከገዙበት ዋጋ በታች ደረሰኝ ማቅረባቸው፣ እንዲሁም አስመጪዎች ከገዙበት ዋጋ በላይ የሚያሳይ ደረሰኝ ማምጣታቸው፣ ከአገሪቱ ለሚያፈተልከው ካፒታል ዓይነተኛው መሣርያ ስለመሆኑ ሪፖርቱ በጥልቀት ቃኝቶታል፡፡ በአንፃሩ የተገላቢጦሹን ማለትም ላኪዎች ከገዙበት ዋጋ በላይ፣ አስመጪዎችም ከገዙበት ዋጋ በታች አግባብነት የሌለው የግብይት ደረሰኝ ቢያቀርቡ ግን የወጣውን ካፒታል መልሶ ለማግኘት እንደሚረዳ ጥናቱ ይጠቁማል፡፡

ከዚህ አኳያ ኢትዮጵያ አግባብነት በሌላቸው የግብይት ደረሰኞች ከመጎዳት ይልቅ ተጠቃሚ የሆነችበት አጋጣሚ መፈጠሩ የተመለከተው 7.1 ቢሊዮን ዶላር ወደ አገሪቱ ገቢ መሆኑን የሚያመላክት መረጃን በማስደገፍ ሲሆን፣ አጋጣሚው የተፈጠረውም ለወጪ ንግድ ከመሸጫ ዋጋ በላይ ለገቢ ንግዱም ከመግዣ ዋጋ በታች ደረሰኞች ለግብይት በመዋላቸው ነው፡፡ በተለይ ከተገዙበት ዋጋ በታች የሚቀርቡ ደረሰኞች ዋና አስተዋጽኦ እንዳላቸው ይታመናል፡፡ በተጨማሪም አገሪቱ በይፋዊ የክፍያ ሚዛኗ (የአገሪቱ ብድር ዕዳና ያበደረችው መጠን) ባታሳየውም ስድስት ቢሊዮን ዶላር የሚገመት ሐዋላ ተመልሶ ወደ አገሪቱ መግባቱ ተጠቅሷል፡፡

ጥናቱን ያካሄደው የማሳቹሴትስ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ኢኮኖሚ ምርምር አንስቲትዩት እንደሚያብራራው፣ የካፒታል ሽሽትን በሚመለከት ከዚህ ቀደም በተደረጉ ጥናቶች የቀረቡ አኀዞች መሠረታውያኑን የተዛቡ የንግድ ግብይት ሰነዶችን እንዲሁም ሐዋላን ያላካተቱ በመሆናቸው ትክክለኛውን አኀዝ አያመለክቱም፡፡ ከዚህ ቀደም የተደረጉ ጥናቶች ከአንድ አገር በሚወጣውና በሚገባው የካፒታል ፍሰት መጠን መካከል ያለውን ልዩነት መሠረት አድርገው ይቀርቡ የነበሩ በመሆናቸው፣ ኦፊሴላዊ ባልሆነ መንገድ በመካሄድ ከሰሐራ በታች ባሉ አገሮች ቁልፍ ሚና ያላቸውን የሐዋላና አግባብነት የጎደላቸው የግብይት ሰነዶችን በካፒታል ፍሰቱ ውስጥ አለማካተት የቀደምት ጥናቶች ደካማ ጎን መሆኑን ተቋሙ በሪፖርቱ አመላክቷል፡፡
Reporter News Paper

Saturday 3 November 2012

ፓርኪንግ ፓርኪንግ

አሜሪካን ሀገር ወደሚኖሩ ወዳጆቼ ቤት ሄጄ ነበር፡፡ ከተጋቡ ሁለት ዓመት ሆኗቸዋል፡፡ ቤታቸው ስገባ የቤቱም ዕቃ የቤቱም ሰዎች ዝምታ ውጧቸዋል፡፡ አባ አጋቶን ቤት የገባሁ ነው የመሰለኝ፡፡ እርሱ ክፉ ላለመናገር ሰባት ዓመት ድንጋይ በአፉ ጎርሶ በአርምሞ ተቀምጧል፡፡ ነገር ዓለሙ አላምር ሲለኝ ‹ምነው ያለ ወትሯችሁ ዝምታ ዋጣችሁ› ብዬ ተነፈስኩ፡፡ እዚህ ቤት የነበረውን ሳቅና ጨዋታ ስለማውቀው፡፡ ‹ሳቅና ጨዋታ ዝና ካማራችሁ› ሲባል አልሰማችሁም፡፡ የመለሰልኝም የለ፡፡ በኋላ ነገሩን ሳጠናው ሁለቱም ተኳርፈዋል ለካ፡፡ ‹‹ለመሆኑ እንዲህ ሳትነጋገሩ ስንት ጊዜ ተቀመጣችሁ› ብዬ ስጠይቅ ስድስት ወር ሆኗቸዋል፡፡ ሁሉም በየሥራው ይውላል፤ ማታ ይመጣል፤ ኪችን ገብቶ ያበስላል፤ በልቶ ቴሌ ቭዥን ያያል፤ ከዚያም ይተኛል፡፡ ቢል ሲመጣ ይህንን እኔ ከፍያለሁ ብሎ አንዱ ወረቀት ጽፎ ይሄዳል፤ ሌላው በተራው ይከፍላል፡፡ ይቺ ናት ትዳር፡፡

ድሮ የሰማሁትን ቀልድ ነበር ትዝ ያሰኙኝ፤ ባልና ሚስቱ ተኳርፋው አይነጋገሩም አሉ፡፡ ቤቱ እንደ መቃብር በጸጥታ ተውጦ ከርሟል፡፡ አንድ ቀን ባል ሌሊት አሥር ሰዓት የሚነሣበት ጉዳይ ገጠመው፡፡ ከተኛ መነሣት የሚከብደው ቢጤ ነበርና የመቀስቀሻውን ሰዓት ሊሞላ ሲስበው ተበላሽቷል፡፡ አዘነም፤ ተናደደም፡፡ ምን ያድርግ፡፡ ባለቤቱ ገና ከሥራ አልገባችም፡፡ ‹የወደዱትን ሲያጡ የጠሉትን ይመርጡ› ነውና፡፡ በቁራጭ ወረቀት ላይ ‹አሥር ሰዓት ላይ ቀስቅሽኝ› ብሎ ጽፎ በራስጌው ባለው ኮመዲኖ ላይ አስቀመጠና ተኛ፡፡ ሚስቱ ስትመጣ አየችውና ስቃ ተኛች፡፡ ልክ ከሌሊቱ አሥር ሰዓት ነቃችና በዚያው በቁራጭ ወረቀት ላይ ‹አሥር ሰዓት  ሆኗልና  ተነሣ› ብላ  ጽፋለት  ተኛች፡፡  እርሱ  ዕንቅልፉን  ለጥጦ  ለጥጦ  ሲነሣ ነግቷል፡፡  ተናደደ፤  ግን እንዳይናገራት ለካስ ተኳርፈዋል፡፡ እዚያው ወረቀት ላይ ‹በጣም ታሳዥኛለሽ› ብሎ ጻፈላት፡፡ 

ራዕይ የሌለው መሪ አልመርጥም! (እናንተስ?)

“የቁርጠኝነት ችግር የለብንም፤ የትኩረት እንጂ”

በአሁኑ ጊዜ በቴሌቪዥን መስኮት ብቅ የሚሉ የመንግስት ባለስልጣናትና ካድሬዎች እንዲሁም የኢህአዴግ አባላት እንደ ፋሽን የያዙትን አነጋገር ሳታውቁት እንደማትቀሩ እገምታለሁ፡፡ ሁሉም ምን ይላል መሰላችሁ? “የመለስን ራዕይ ለማሳካት …” ብሎ ይጀምርና ይሄንኑ አባባሉን በየመሃሉ እየሸነቆረ ትክት አድርጐን ይሄዳል፡፡ ሰሞኑን አንዷ የመንግስት ሠራተኛ “ጠዋት ቀደም ብዬ ሥራ እገባለሁ፤ ማታ እስከ 11 እና 12 ሰዓት ቆይቼ እሰራለሁ” ስትል ተናገረች (“አበጀሁ” ያለችው ማን ነበረች?) ጉዱ የሚመጣው “ለምን ትሰራለች?” የሚል ጥያቄ ስትጠይቁ ነው፡፡ ይሄን ሁሉ የምትሰራው እኮ “የመለስን ራዕይ ለማሳካት” ነው፡፡
 
ግን እኮ እሳቸው ከ8 ሰዓት በላይ የማሰራት ራዕይ የነበራቸው አይመስለኝም፡፡ (ያለ ክፍያ ከሆነ እኮ የጉልበት ብዝበዛ ነው) ቆይ ግን “አዳሜ” የራሱ ራዕይ የለውም እንዴ? የመንግስት መሪዎችም ቢሆኑ እኮ “የመለስ ራዕይ” ላይ የራሳቸውን ጨምረው ካላጐለበቱት ብዙም የሚያዛልቅ አይደለም፡፡ “ድህነት ጠላታችን ነው” ብሎ መዋጋት የመለስ ራዕይ ነው ቢባል ተገቢ ነው፡፡ የህዳሴ ግድቡንም የመለስ ራዕይ ነው ብሎ ለስኬቱ መታተር ስህተት የለውም፡፡ በሰበብ አስባቡ “የታላቁን መሪ” ስም መጥራት ግን ተገቢ አይደለም (አረፍ ይበሉበት እንጂ!) እንዴ አንዳንዴ እኮ ራስን ችሎ መቆምም ያስፈልጋል፡፡ እንደውም የኢህአዴግ መሪዎች ከመለስ ራዕይ ውጭ የራሳችሁ ራዕይ ምንድነው ቢባሉ የሚመልሱትን ማወቅ እፈልጋለሁ፡፡ “የራሳችን ራዕይ የለንም” ካሉ ግን በ2007 ምርጫ ያገናኘን ብዬ አልፋቸዋለሁ፡፡ በድምፄ ጉድ እሰራቸዋለሁ (ዛቻ እኮ አይደለም!) ራዕይ የሌለው መሪ አልመርጥማ! (እናንተስ?)  እኔ የምለው … መዲናችን ልደቷን እያከበረች ነው የሚባል ነገር ሰማሁ ልበል (የትኛውን ልደት?) አምና 125ኛ ዓመቷን አከበረች አልተባለ እንዴ? አንዱ ወዳጄን ስጠይቀው ምን አለኝ መሰላችሁ … “እያረፈች ማክበር አትችልም?” ወቸ ጉድ … ደሞ ልደት ለማክበር የምን ማረፍ ነው! እሺ ማክበሩንስ ታክብር … ግን ስንተኛ ዓመቷን ነው የምታከብረው? ቆይ አዲስ አበባም ዕድሜዋን መደበቅ ጀመረች እንዴ? (“የወንድ ደሞዝና የሴት ዕድሜ አይጠየቅም” አሉ) ግን እኮ አምና 125ኛ ዓመቷ ከሆነ ዘንድሮ 126ኛ ዓመቷን መሆን አለበት! (ቀላል የማቲማቲክስ ስሌት ነው!)

Friday 2 November 2012

በህልሜ!

ከመሃመድ ሀሰን

40-60 ቤት ለመመዝገብ ሳር-ቤት አካባቢ ቀበሌ 03 ተሰልፍያለሁ፡፡ ትከሻዬን ሲከብደኝ ከኃላዬ የተሰለፈውን ሰው ለማየት ዞርኩኝ፡፡ አቶ ኃይለማርያም ናቸው፡፡ ክው አልኩኝ!

‹‹ምነው በሰላም ነው?›› አልኳቸው የተረጋጋሁ ለመምሰል እየሞከርኩ፡፡

‹‹በሰላም ነው...ያው ለ40-60 የቀበሌ መታወቂያ ለማሳደስና ቤት አልባ መሆኔን ማረጋገጫ ለማውጣት ነው፡፡›› ‹‹አንተስ?›› አሉኝ፡፡

‹‹እኔም እንደዚያው ነው››

‹‹ወረፋ ታስቀድመኛለህ!? በጠዋት ቤተመንግስት የቀጠርኳቸው አምባሳደሮች ስላሉብኝ ነው...! ››

‹‹ይቅርታ እኔ ራሴ ክላስ ትቼ ነው የመጣሁት እቸኩላለሁ›› አልኳቸው፡፡

‹‹ምን ይሻላል ባካችሁ!›› ብለው ተከዙ፡፡ ሲተክዙ ወደሰማይ አንጋጠው በመሆኑ ርዕይ የሚያዩ ይመስላሉ፡፡

‹‹የት ነው የምትሰራው?››

‹‹መቀሌ አስተማሪ ነኝ፡፡››

‹‹እርስዎስ?››

‹‹እኔም አርባምንጭ አስተማሪ ነበርኩ፡፡ አሁን እንኳ ጠቅላይ ሚኒስትር ለመሆን ክፍት የስራ ቦታ ወጥቶ እዛ ገብቻለሁ፡፡ በቲቪ አይተኸኝ አታውቅም?

‹‹ኸረ እኔ ቲቪ አላይም...››

‹‹እውነትህን ነው?››

‹‹ምን አስዋሸኝ፡፡ ረዥም ጊዜ ነው ቲቪ ካየሁ....እና ....አዲሱ ስራ አሪፍ ነው? ወደዱት?››

‹‹ምንም አይልም፣ ትንሽ ስራ ይበዛዋል፡፡ እንደ ዩኒቨርሲቲ ነጻነት የለውም፡፡ በጌታ ፍቃድ እወጠዋለሁ ብያለሁ››

‹‹መበርታት ነው እንግዲህ›› አልኳቸው፡፡

‹‹እኔ ምልህ ቤቱ በስንት ዓመት የሚደርሰን ይመስልሀል?››

‹‹ቶሎ የሚደርስ እንኳ አይመስለኝም፡፡ ግን ከዚህ በፊት ኮንዶሚንየም ሳልመዘገብ ስላመለጠኝ በድጋሚ እንዳልጸጸት ብዬ ነው የምምዘገበው››

‹‹እሱስ እውነትህን ነው፡፡ እኔ ምልህ! አራት ኪሎ አካባቢ ኮንዶሚንየም ኪራይ ይገኛል እንዴ ? ከስራዬ ጋር እዚያ አካባቢ ባገኝ ይቀርበኝ ነበር››

‹‹አራት ኪሎ ቱሪስት ጀርባ ኮንዶሚንየሞች አሉ መሰለኝ፡፡››

‹‹ስንት ይሆናል?››

‹‹ባለ ሁለት መኝታ እስከ 4ሺህ 500 አይሆንም ብለው ነው?››

‹‹በእየሱስ ስም!›› ደሞዜ ራሱ 6ሺ አይሞላም እኮ፡፡ ምን በልቼ ልኖር ነው?››

እንደምንም ማብቃቃት ነው እንግዲህ፡፡ ወይም ለምን ቀበና አካባቢ አይከራዩም፤ ዋጋ ረከስ ይላል፡፡ ለአራት ኪሎም ቅርብ ነው፡፡

‹‹እውነትህን ነው...ቀበና ጥሩ ሳይሆን አይቀርም፣ ባለ አራት መኝታ እዚያ አካባቢ ስንት አገኛለሁ?››
ከት ብዬ ሳቅሁ፡፡ ‹‹ባለ አራት መኝታ የሚባል ኮንዶሚንየም የለም፡፡ እየቀለዱ ነው አይደል?››

ኖኖ! እንዴት በዚህ ዘመን እቀልዳለሁ፡፡ ለምንድነው የሌለው?

‹‹አልተሰራማ!›› አልኳቸው፡፡

‹‹ለምን አልተሰራም?››

‹‹እኔ ምን አውቄ! አራት ኪሎ ነው የምሰራው አላሉም እንዴ! እርሶ ይንገሩኝ እንጂ፡፡››

‹‹አንተ ደሞ! ገና ስራ መጀመሬ ነው አልኩህ እኮ! ሶስት ሳምንትም አልሞላኝ፡፡››

‹‹ሁለት መኝታ ታዲያ ጥሩ እኮ ነው፣ አይበቃዎትም?፡፡››

ሶስት ሴት ልጆች አሉኝ፣ በሁለት መኝታ እንዴት ተኩኖ ይኖራል?

‹‹ያው ማብቃቃት ነው!››አልኳቸው፡፡

‹‹እኔ ምልህ!?ይሄ ሁሉ ግን ቤት የሌለው ነው?›› ነው እያጋነኑ ነው? እንዲህ ከሆነማ ቤት የሌለውን ከሚመዘገቡ ቤት ያላቸውን ቢመዘግቡ ለአሰራር ይመች ነበር፤ አይመስልህም?፡፡››

‹‹ትክክል ብለዋል!››

‹‹በዚህ ወረፋ ከሰዓትም የሚደርሰኝ አይመስለኝም!›› 4ኪሎ ደርሼ ብመለስ ይሻላል፡፡

‹‹ይቅርብዎ!ታክሲ አያገኙም፡፡ እዚሁ ተሰልፈው ቢጠብቁ ነው የሚሻልዎት››

‹‹አይ...የሚያደርሰኝ መኪና አለ›› ነጫጭ 3 ኮብራዎችን ከርቀት አሳዩኝ፡፡ ሌሎች ሶስት ጥቁር መነጽር ያደረጉ ወጠምሻዎች መኪናዎቹ ዙርያ ፈንጠርጠር ብለው ቆመዋል፡፡ ወደኔ እያዩ ገለማመጡኝ፡፡

‹‹ምንድናቸው እነዚያ››

‹‹ጠባቂዎቼ ናቸው››

‹‹ከምንድነው የሚጠብቅዎት?››

ፈገግ አሉ! ለመጀመርያ ጊዜ ፍንጭት መሆናቸውን አየሁ፡፡

Thursday 1 November 2012

የማሌዥያ ኩባንያ እርሻ በሱርማ ማኅበረሰብ ተጠቃ

 
በደቡብ ክልል ቤንች ማጂ ዞን የፓልም ዘይት ለማምረት 31 ሺሕ ሔክታር መሬት የወሰደው የማሌዥያ ኩባንያ በሱርማ ማኅበረሰብ በተደጋጋሚ በሚደርስበት ጥቃት ሥራውን በአግባቡ መሥራት እንዳልቻለ ተገለጸ፡፡ ለኩባንያው የተሰጠው የሳር መሬት ሲሆን ከብት አርቢ የሆነው የሱርማ ማኅበረሰብ ቦታውን ለግጦሽ ይጠቀምበታል፡፡

የፌዴራል መንግሥት ከደቡብ ክልል መንግሥት ጋር በመቀናጀት የሱርማን ማኅበረሰብ ከአርብቶ አደርነት ወደ አርሶ አደርነት ወይም ወደከፊል አርሶ አደርነት መቀየር የሚያስችል ዕቅድ አውጥቷል፡፡

ይህንን ዕቅዱን ለማስፈጸም 17 ሺሕ ቤቶችን ገንብቶ ለሱርማ ማኅበረሰብ አካላት ለማከፋፈል የሚያስችለውን ሥራ መጀመሩን የቤንች ማጂ ዞን የኢንቨስትመንት ማስፋፋት የሥራ ሒደት ባለቤት አቶ በላይ አበበ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

የሪፖርተር ምንጮች እንደገለጹት፣ አንድ የሱርማ አርብቶ አደር ከ600 በላይ ከብቶች ይኖሩታል፡፡ እነዚህን ከብቶች ይዞ ውኃና ሳር ወዳለበት አካባቢ እንደ ወቅቱ ሁኔታ ይዘዋወራል፡፡

ለማሌዥያው ሊምሲዩጃን ኩባንያ የተሰጠው መሬት የሱርማ ማኅበረሰብ ለግጦሽ የሚጠቀምበት የሳር መሬት ነው፡፡

ሊምሲዩጃን ያካሄዳቸው የእርሻ ሥራዎች በማኅበረሰቡ ተደጋጋሚ ጥቃት እየተሰነዘረባቸው ነው፡፡ ባለፈው ረቡዕ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ በሰበሰቡት የኢንቨስተሮች ስብሰባ የኩባንያው ተወካይ ይህንኑ አረጋግጠዋል፡፡

ተወካዩ እንዳሉት፣ የሱርማ አርብቶ አደሮች የሚያካሂዱትን ልማት በተደጋጋሚ አጥቅተዋል፡፡ ችግሩም ከበድ ያለ በመሆኑ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ መፍትሔ እንደሚፈልጉ ጨምረው ገልጸዋል፡፡

አቶ ኃይለ ማርያም ለኩባንያው በሰጡት አስተያየት፣ የሱርማ ማኅበረሰብ ጥቃቱን ያደረሰው ኩባንያው የሚያካሂደው ሥራ እንደሚጠቅመው ግንዛቤ እንዲጨብጥ ባለመደረጉ ነው፡፡ ግንዛቤ እንዲጨብጥ ቢደረግ ከማንም በበለጠ ፕሮጀክቱን ይደግፋል ሲሉ አቶ ኃይለ ማርያም በአንድ ወቅት በአካባቢው ያጋጠማቸውን በመጥቀስ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

የማሌዥያው ኩባንያ ከሁለት ዓመት በፊት ወደ ኢትዮጵያ ሲመጣ ለፓልም ዘይት ልማት የጠየቀው 100 ሺሕ ሔክታር መሬት ነበር፡፡

ኩባንያው በዚህ መሬት ላይ የፓልም ዛፎችን በመትከል የምግብ ዘይት የማምረት ዕቅድ ይዟል፡፡ ነገር ግን መንግሥት የጠየቀውን መሬት በአንድ ጊዜ አላቀረበለትም፡፡ ምክንያቱም እንደ ሥራው አፈጻጸም እየታየ የጠየቀው መሬት ሊሰጠው ይገባል ከሚል አስተሳሰብ መሆኑን አቶ በላይ ገልጸዋል፡፡

ኩባንያው በአሁኑ ወቅት 31,299 ሔክታር መሬት ተሰጥቶታል፡፡ ይህንን ፕሮጀክት ለማካሄድ 3.72 ቢሊዮን ብር ካፒታል አስመዝግቧል፡፡

Monday 29 October 2012

Er ikke jeg et menneske?


Lønseth forsikrer om forsvarligheten. Arbeiderpartiet, Høyre og Fremsittspartiet nikker bak muren. De andre” er tittelen på Margreth Olins film- er det i realiteten vi som er i ferd med å bli fremmede fra oss selv?
Jeg har sett filmen De andre. De andre vandrer gjennom verden, går gjennom piggtråden, barna som ikke er barn, men flyktninger og pasienter. De blir skutt, de drukner, de dør på veien til Norge. De ligger sammenkrøpet i bager. De slår hodet i murveggen i Norge. Barn som tenker på døden. Gutten som torturerer seg selv for ikke å frykte tortur. Gutten som er far og beskytter for sin stygt skadde lillebror. Jeg lever for å hjelpe min bror. Bare Gud hjelper meg. En gutt spør: Er ikke jeg et menneske? Asylpolitisk collage. Svart mugg oppover veggen i Drammen. Stønad under fattigdomsgrensen etter avslag, utsulting, nekting av helsehjelp til torturerte, nekting av retten til å arbeide, ungdom nektes videregående, ikke rett til barnehage. Barn vokser opp og skades psykisk på asylmottak. Lønseth forsikrer om forsvarligheten. Arbeiderpartiet, Høyre og Fremskrittspartiet nikker bak muren. Tybring Gjedde skriver: ”I det øyeblikket Hassan i filmen utbasuner, med referanse til norske myndigheter; «jeg forstår ikke hvordan de kan behandle et menneske slik», da mister jeg sympatien. Akkurat da blir Hassan irrelevant for meg.” Er ikke jeg et menneske. Vi vil skremme alle med avslag, sier politiet. Vi trapper opp aksjonene framover, ingen med avslag skal kjenne seg trygge. De skremte skal skremmes. Det virker, de kan ikke sove lenger. Etiopia, Somalia, Iran, Irak, Palestina og Afghanistan. Norge kjempers fødeland, Norge i rødt hvitt og blått, Norge mitt Norge. Små barn også under skolealder fengsles i Norge, på Trandum utlendingsinternat. Barn skal ikke sitte i fengsel, asylbarna skal. Politisk vedtatt med bred støtte. Det er nylig utvidet lovhjemmel for fengsling av flyktninger ved mistanke om at de kan unndra seg utsending, avdelingen for familier med barn bygges ut. Er ikke jeg et barn. Det er praktisk at utlendingsfengselet ligger så nært rullebanen at flyktningene om nødvendig kan kjøres rett på flyet, uten omveien via Gardermoen. 70 politifolk mot 8 asylsøkere med avslag nordpå, ingen vet om barn var involvert, ingen vet om barn så de 70 svartkledde ta de 8 bakbundet ut i bilene. Mange på mottaket var ikke klar over at de hadde avslag. Utlendingspolitiet skal selv sørge for at utlendingene innesperret på Trandum får helsehjelp, det har politikerne sikret ved forskrift, med stødig humanisme. Selvmord på mottak registreres ikke i Norge, etter sigende på grunn av personvernshensyn. Har ikke jeg et liv. ”De andre” er tittelen på Margreth Olins film- er det i realiteten vi som er i ferd med å bli fremmede fra oss selv?

Sunday 28 October 2012

ይህ ጊዜ

በታሪካችን ውስጥ ያለው የጊዜው ዕንቆቅልሽ ህንፃዎቻችን ረዥም መሆናቸውና ትዕግስታችን ማጠሩ መንገዶቻችን ሰፊ መሆናቸውና አመለካከታችን መጥበቡ ነው   

ብዙ ገንዘብ እናጠፋለን ግን ያለን ትንሽ ነው  ብዙ እንገዛለን ግን እርካታችን ዝቅተኛ ነው ትላልቅ ቤቶች አሉን ግን ቤተሰቦቻችን ትንሽ ናቸው  የተመቻቹ ሁኔታዎች አሉ ግን የጊዜ እጥረት አለብን

ብዙ ዲግሪ አለን ግን ዝቅተኛ ምክንያታዊነት አለን  እውቀታችን ብዙ ነው ነገር ግን ግምታችን ዝቅተኛ ነው  ብዙ አዋቂዎች ቢኖሩንም ችግራችን ብዙ ነው  ብዙ መድሀኒቶች አሉን ግን ፈውሳችን ዝቅተኛ ነው  

ብዙ እንጠጣለን ብዙ እናጨሳለን  በግድ የለሽነት ገንዘብ እናጠፋለን  የምንስቀው ግን ትንሽ ነው በፍጥነት መኪና እንነዳለን  በቀላሉ እንናደዳለን አርፍደን ነው የምንተኛው ተዳክመን ከእንቅልፍ እንነቃለን  ትንሽ ነው የምናነበው ቴሌቪዥን ብዙ እናያለን ብዙ ግን አንፀልይም 

ሕይወታችንን ማራዘም ችለናል ግን ኑሯችንንን ናሳጥራለን  ወደ ጨረቃ ተጉዘን ተመልሰናል ነገር ግን መንገድ ቋርጠን ዲስ ጎረቤት ለማየት ንቸገራለን  የውጭውን ለም ተቆጣጥረናል ውስጣችንን ግን ልተቆጣጠርነውም ::  

ትላልቅ ነገሮችን ሰርተናል ነገር ግን የተሻሉ ነገሮችን አልሰራንም አየሩን አፅድተናል ነገር ግን መንፈሳችንን በክለናል አቶምን ተገንዝበናል ነገር ግን ወገናዊነትን አልተገነዘብንም  ብዙ እንፅፋለን ግን ትንሽ ነው የምንማረው

የምናቅደው ብዙ ሲሆን የምንፅፈው ግን ትንሽ ነው መጣደፍን ተምረናል ነገር ግን መታገስን ልተማርንም  ብዙ መረጃዎችን የሚይዙና ከምንፈልገው በላይ ብዙ ኮፒ የሚያደርጉ ኮምፒተሮች ሰርተናል ነገር ግን የርስ በርስ ግንኙነታችን ዝቅተኛ ነው 

ይህ ዘመን ምግብ በቅፅበት የሚገኝበትና የበላነው ምግብ ቶሎ የማይፈጭበት ዘመን ነው  ይህ ዘመን የታላላቅ ሰዎች ግን የዘቀጠ ፀባይ  የከፍተኛ ትርፍ ግን የአልባሌ ግንኙነት ዘመን ነው  ይህ ዘመን እጥፍ ድርብ የቤተሰብ ገቢ ነገር ግን ብዙ ፍች የደልቃቃ ቤቶች ግን የሀዘንተኛ ኗሪዎች ዘመን ነው ::  

እነዚህ ጊዜዎች ጉዞ ቅፅበታዊ የሆነበት  የህፃናት መፀዳጃ ጨርቆች ተጠቅመን የሚጣሉበት የቆሸሸ ግብረ ገብነት  የአንድ ሌሊት ወሲባዊ ግንኙነት ብዙ ወፍራም ሰዎች ያሉበት  ጉደኛ የሆኑ ኪኒኖች ባንድ ጊዜ ሊያስደስቱን ዝም ሊያሰኙን ወይንም ሊገሉን የሚችሉበት ጊዜ ነው 

ይህ መጋዘን ውስጥ ምንም ነገር ሳይኖር ለህዝብ በማሳያው ክፍል ውስጥ ብዙ ዕቃ የሚቀርብበት ጊዜ ነው 
ይህ ጊዜ ቴክኖሎጂ ዕንዲህ ያለውን ጽሁፍ አምጥቶልን ሀሳቡን ከሌሎች ጋር ለመካፈል የምንወስንበት ወይንም መሰረዣውን "ዲሊት " የሚለውን ቁልፍ ተጭነትን
መልዕክቱን የምናጠፋበት ጊዜ ነው ::    
                      ________________

የንግግር ጥበብ

የንግግር ጥበብ አንድ ብዙ ማውራት የሚወድ ወጣት ወደ ፈላስፋው ሶቅራጥስ ዘንድ በመሄድ ‹‹የንግግር ጥበብ›› እንዲያስተምረው ይጠይቀዋል፡፡ ፈላስፋውም ‹‹አንተን የማስከፍልህ ሌሎች ከሚከፍሉት በእጥፍ ነው›› አለው፡፡ ወጣቱም በመደነገጥ ስሜት ‹‹እጥፍ የምታከፍለኝ ምክንያቱ ምንድን ነው?›› ብሎ ጠየቀው፡፡ ሶቅራጥስም ‹‹አንተን የማስተምርህ ሁለት ዓይነት ጥበብ ነው፡፡ አንደኛው የንግግር ጥበብ ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ የማዳመጥ ጥበብ ነው፡፡ የሁለተኛው ግን ከመጀመርያዋ ይበልጣል በማለት መለሰለት፡፡

ማዳመጥ ትልቁ የንግግር ጥበብ ነው ፈጣሪ መናገር እንድንችል ምላስ ብቻ ሳይሆን ማዳመጥ እንድንችልም ጆሮ ሰጥቶናል፡፡ ንግግራችን የተሟላ እንዲሆን የግድ ማዳመጥ አለብን፡፡ ሌላው ቢቀር ተናግረን መሰማታችንን ማወቅ የምንችለው ሌላውን ማዳመጥ የቻልን እንደሆነ ብቻ ነው፡፡ አንድ ምላስ ሁለት ጆሮ ሲሰጠን በራሱ ምክንያት አለው፤ ‹‹በመጠን ተናገሩ በብዛት አድምጡ›› የሚለውን መልእክት ለማስተላለፍ ብቻ ሳይሆን ብዙ ከመናገራችን በላይ ብዙ ማዳመጥ አለመቻላተን ታላቅ ጉዳት እንዳለውም ለማስገንዘብ ነው፡፡ በመልካም አስተሳሰብ የተሞላ አስተዋይ ሰው ከመናገሩ በፊት ያስባል፤ መቼ መናገርና መቼ ዝም ማለት እንዳለበትም ያውቃል፡፡ ሲናገር ‹‹በመጀመርያ ብዙ ከማውራት ይልቅ ብዙ ማዳመጥን እመርጣለሁ፡፡ መናገር ባስፈለገኝ ጊዜ ቃላቶቼ በከናፍርቶቼ በኩል ከመውጣታቸው በፊት ረጋ ብዬ እመዝናቸዋለሁ›› በማለት ተናግሯል፡፡

ማዳመጥ ለመስማት መፈለግ ነው  ፈላስፋውና የሒሳብ ሊቁ ብሌዝ ፓስካል ሲናገር ‹‹አንድ የደረስኩበት ነገር አለ፤ እርሱም የሰው ልጅ ሁሉም ክፋቶች የሚመጡት በውስጡ ዝም ማለት አለመቻሉ ላይ ነው፤›› ብሏል፡፡ ራሳቸውን የሚገዙ ሰዎች በማዳመጥ ችሎታቸው ከፍተኛ ደረጃ የደረሱ ናቸው፡፡ ጤናማ ቃልን የሚናገሩና አንደበታቸው ክፉ ቃል እንዳይወጣቸው የሚገቱ ሲሆኑ ዓለምን ለማሸነፍ ከመውጣታቸው በፊት ራሳቸውን ማሸነፍ የሚችሉ ናቸው፤ አስቀድመው ስለራሳቸው በደንብ ያውቁ ስለሆኑ የኩራትና የትዕቢትን ካባ ከላያቸው ላይ አውልቀው የጣሉ ናቸው፡፡ ሰዎችን በመስማትና በማዳመጥ መካከል ከፍተኛ ልዩነት አለ፡፡ ሰዎች ብዙ ሥልጣን እያገኙ ሲሄዱ ከእነርሱ በታች ያሉትን ለማድመጥ ትዕግሥት እያጡ ይሄዳሉ፡፡ የተደፈነ ጆሮ ለተዘጋ ጭንቅላት የመጀመርያው መገለጫ ነው፡፡

በተናገርነው እንጂ ዝም ባልነው መቼም አናፍርም
ብዙ ጊዜ እንወደዳለን ብለው የሚናገሩ ሰዎች ከመፈቀራቸው በተቃራኒ ጥላቻን አትርፈዋል፡፡ ፈላስፋው ፕሉታርክ እንዲህ ዓይነት ሰዎችን ሲገልጻቸው ‹‹በመናገራቸው ብዛት መወደድ የሚፈልጉ ይጠላሉ፤ እናስደስታለን ብለው ሲጠብቁ ይሰለቻሉ፡፡ እንደነቃለን ብለው ሲጠብቁ መሳቂያ ይሆናሉ፡፡ እንደነዚህ ዓይነት ሰዎች ወዳጆቻቸውን ሲጎዱ ጠላቶቻቸውን ደስ ያሰኛሉ፡፡ በመጨረሻም ራሳቸውን በራሳቸው ያጠፋሉ›› ብሏል፡፡

ከብዙ ንግግር ብዙ ስህተት ይገኛል እውነተኛ ማዳመጥ ውስጣዊ ነው፡፡ አንድ ንግግርን ከውስጣችን በደንብ ካዳመጥን ያዳመጥነው ከልባችን ጋር ይዋሃዳል፡፡ ፈላስፋው ፕሉታርክ ‹‹ማዳመጥ እውነተኛ የሆነ ሕይወት የመኖር ጥበብ ነው›› ብሏል፡፡
ማዳመጥ ጆሮን መክፈት ሳይሆን
ልብን መክፈት ነው፡፡ ማዳመጥ ከማይችል ሰው ጋር መወያየት እጅግ ከባድ ነው፡፡ ሁለት ሰዎች በደንብ መነጋገር ከፈለጉ ከሁለቱ አንደኛው ማዳመጥ ይኖርበታል፡፡ የብዙዎች ችግር ማዳመጥ አለመቻላቸው ሳይሆን እየተቻላቸው ሌሎችን ማዳመጥ አለመፈለጋቸው ነው፡፡ እንዲህ ዓይነት ሰዎች የሚያዳምጡ ይመስላሉ እንጂ የሚያዳምጡት ራሳቸውን ነው፡፡

የሥነ አእምሮ ሐኪሞች አእምሮው የታመመን ሰው ለማከም ትልቁ መንገድ መድኃኒተ መስጠት ወይም የሥነ ልቦና ምክርን መለገስ ብቻ ሳይሆን ልብን ሰጥቶ ማዳመጥ ከፍተኛ ቦታ እንዳለው ይናገራሉ፡፡ በአሁኑ ጊዜ ሰው ያጣው የሚያወራለትን ሳይሆን የሚያዳምጠውን ነው፡፡ ብዙ ሰዎች በልባቸው ውስጥ የሞላውን፣ ከወስጥ የሚሰማቸውን ጭንቀትና ሰላም ማጣት ሲገልጹ ልቡን ከፍቶ የሚያዳምጣቸው ሰው ይፈልጋሉ፡፡ ከመናገር በላይ ማዳመጥ የንግግር ጥበብ መሆኑን ማስተዋል ትልቅ ጥበብ ነው፡፡

ጥሩ የንግግር ችሎታ ያላቸው ሰዎች
ጥሩ የማድመጥ ችሎታ ያላቸው ናቸው፡፡
- ዳንኤል ዓለሙ (የምሕረት ልጅ) ‹‹ራስን የመለወጥ ምሥጢር››