Monday 17 June 2013

ጫትና ሺሻ በአዳማ ከተማ ለሴተኛ አዳሪነት መስፋፋት ምክንያት እየሆኑ ነው ተባለ

በአዳማ ከተማ  የጫት መሸጪያ ሱቆች በከፍተኛ ደረጃ እተስፋፉና የቃሚውም  ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ ነው ተባለ  መኖሪያ ቤቶችን ጨምሮ ከመለስተኛ አንስቶ እስከ አለም አቀፍ ሆቴሎች ድረስም በዚህ የጫት ማስቃምና የሺሻ ማስጨስ ተግባር ውስጥ በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ የከተማው ነዋሪዎች ልጆቻችን በዚህ ችግር ውስጥ እየወደቁ ነው በዚህ ምክንያትም ለጎዳና ተዳዳሪነት የሚዳረጉና የታዳጊ ህፃናት ሴተኛ አዳሪነትም በከተማዋ እየተስፋፋ ነው ይላሉ አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጠው በማሳሰብ።በዚህ ችግር ውስጥ የአዳማ ዩንቨርስቲ ተማሪዎችም ግንባር ቀደም ተሳታፊ እየሆኑ መምጣታቸው ጉዳዩን አሳሳቢ አድርጎታል ይህ የጫት አቅርቦት ጉዳይ የአዳማ ዩንቨርስቲን ጨምሮ በከተማው በሚገኙ ኮሌጆችና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አቅራቢያ ጭምር በብዛት ይስተዋላል በአዳማ አብዛኛዎቹ ሆቴሎች  ውስጥ መቃሚያ ክፍሎችን በማዘጋጀት ለህገ-ወጥ ገቢ ማግኛ መጠቀም የተለመደ ነው ይባስ ብሎም አንዳንድ የከተማዋ  ሆቴሎች ማስታወቂያዎችን ጭምር በመለጠፍ ማስቃሚያ ቦታ እንዳላቸው ያስተዋውቃሉ ቡናውን የሚያፈሉና ሺሻውን ለተጠቃሚዎቹ  የሚያቀርቡት ደግሞ ታዳጊ ሴቶች ናቸው በተለይ አርብ ቅዳሜና እሁድ  ለዚሁ ተግባር ከአዲስ አበባና ሌሎች የአቅራቢያ ከተሞች ወደ አዳማ  የሚገባው ሰው ቁጥርም ከፍተኛ ነው ጉዳዩን አስመልክቶ  የአዳማ ከተማ አስተዳደር  ምክትል ከንቲባ አቶ አህመድ የሱፍ  ችግሩ መኖሩን አምነው ይህም ለከተማዋ ፀጥታ ጭምር አሳሳቢ መሆኑን ያነሳሉ ይህ ጉዳይ ከዚህ በፊት በከተማው አስፋፍቶት የነበረውን ወንጀል በማስታወስ አቶ አህመድ እንደሚሉትና ህብረተሰቡም እንዳነሳው በሆቴል ቤቶች የሚቅሙት  የከተማ አስተዳደሩ ሰራተኞችም ጭምር ናቸው በመሆኑም በዚህ ድርጊት ውስጥ የተገኙ ሰራተኞችን ባለፈው ወር ከስራ አግደናል ይላሉ ምክትል ከንቲባው ይህንን  ችግር ለመፍታትም ትልልቅ ሆቴሎችን ጨምሮ የተለያዩ  ጫት በማስቃም ስራ ላይ ተሰማርተው የሚገኙ አካላትን ፈቃዳቸውን እስከመሰረዝና ከአዳማ ዩኒቨርስቲ ጋር በጋራ መስራት የሚቻልበትን  ሁኔታ ለመጀመር እንቅስቃሴ በመደረግ ላይ ነው ፡፡

Sunday 16 June 2013

የ Big Brother ተወዳዳሪ ቤቲ እናት ልጄ ይህን አታደርግም 100 ፐርሰንት እርግጠኛ ነኝ ምቀኛ ነው እያሉ ነው


መምህራን በሕፃናት ላይ ግብረሰዶም በመፈጸም ወንጀል ተጠርጥረው ተከሰሱ


የዋስትና መብታቸው ተገፎ ማረሚያ ቤት እንዲቆዩ ተደርገዋል
-አካዳሚውም ተገቢ ጥበቃ ባለማድረጉ በክሱ ተካቷል
በቦሌ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ሩዋንዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሚገኘው ካራክተር ሆልማርክ አካዳሚ በሚባል ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ፣ በሁለት ወንድ ሕፃናት ላይ ግብረሰዶም ፈጽመዋል የተባሉ ስድስት መምህራን ተጠርጥረው ክስ ተመሠረተባቸው፡፡
 ተጠርጣሪዎቹ የአካዳሚው ዳይሬክተር አቶ ደሳለኝ ኃይለየሱስ፣ የአካዳሚው ሱፐርቫይዘር አቶ የኔዓለም ጌታቸው፣ መምህር ዓለማየሁ ገብሬ፣ መምህር ደበበ ጥሩነህ፣ አቶ መልካሙ ቀለብና አቶ ሳምሶን መኩሪያ ሲሆኑ፣ አካዳሚው ካራክተር ሆልማርክ አካዳሚ አክሲዮን ማኅበርም መከሰሱን የፌዴራል ዓቃቤ ሕግ ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ለሰባተኛ ወንጀል ችሎት ያቀረበው ክስ ያስረዳል፡፡ 
ተጠርጣሪዎቹ የ10 እና የ11 ዓመት ዕድሜ ያላቸውን ሁለት ወንድ ሕፃናትን ከጥቅምት ወር መጀመሪያ 2005 ዓ.ም. ጀምሮ በምሳና በዕረፍት ጊዜ ተማሪዎች ከክፍል ሲወጡ፣ ወደ ባዶ ክፍል በመውሰድ በተደጋጋሚ እየተፈራረቁ የግብረሰዶም ድርጊት እንደፈጸሙባቸው ክሱ ያስረዳል፡፡ በተለያዩ ጊዜያት ዳይሬክተሩንና ሱፐርቫይዘሩን ጨምሮ ሌሎቹም መምህራንም በየካቲት ወር ሁለት ቀናት፣ እንዲሁም በሚያዝያ ወር በሕፃናቱ ላይ ድርጊቱን ፈጽመዋል በሚል ተጠርጥረው፣ የሕፃናት ክብር ድፍረት ወንጀል ተካፋይ በመሆን መከሰሳቸውን ክሱ ያብራራል፡፡ 
ካራክተር ሆልማርክ አካዳሚ አክሲዮን ማኅበር በሥሩ ያሉትን ሠራተኞችና ኃላፊዎች በአግባቡ መቆጣጠርና የሕፃናትን ጤንነትና አካልን በአግባቡ መጠበቅ ሲገባው ባለመፈጸሙ፣ በወንጀል ድርጊቱ ተካፋይነት ተጠርጥሮ መከሰሱን ክሱ ይገልጻል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ ፍርድ ቤት ቀርበው ድርጊቱን አለመፈጸማቸውን በመግለጽ የዋስትና መብታቸው እንዲጠበቅላቸው ቢጠይቁም፣ ድርጊቱ ከባድ መሆኑን በመግለጽ ፍርድ ቤቱ የዋስትና መብታቸውን ውድቅ በማድረግ፣ የዓቃቤ ሕግ ምስክሮችን ለመስማት ለሰኔ 14 ቀን 2005 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ ተጠርጣሪዎቹም በማረሚያ ቤት እንዲቆዩ አዟል፡፡

http://www.ethiopianreporter.com/index.php/news/item/2189-%E1%88%98%E1%88%9D%E1%88%85%E1%88%AB%E1%8A%95-%E1%89%A0%E1%88%95%E1%8D%83%E1%8A%93%E1%89%B5-%E1%88%8B%E1%8B%AD-%E1%8C%8D%E1%89%A5%E1%88%A8%E1%88%B0%E1%8B%B6%E1%88%9D-%E1%89%A0%E1%88%98%E1%8D%88%E1%8C%B8%E1%88%9D-%E1%8B%88%E1%8A%95%E1%8C%80%E1%88%8D-%E1%89%B0%E1%8C%A0%E1%88%AD%E1%8C%A5%E1%88%A8%E1%8B%8D-%E1%89%B0%E1%8A%A8%E1%88%B0%E1%88%B1

Saturday 15 June 2013

Subcommittee Hearing: Ethiopia After Meles: The Future of Democracy and Human Rights



| 2172 House Rayburn Office Building Washington, DC 20515 | Jun 20, 2013 10:00am

Chairman Smith on the hearing: “Ethiopia is a vital American ally in Africa, but its human rights and democracy policies fall short of the basic rights that Ethiopians deserve. Our hearing will look at the policies of the current Ethiopian government in hopes that it will better accommodate political opposition and civil society, and respect the rights of all Ethiopians.  We also need to consider how the U.S. Government can support ways to improve the rights—and lives—of the Ethiopian people.”

Witnesses

Panel I

The Honorable Donald Y. Yamamoto

Acting Assistant Secretary of State
Bureau of African Affairs
U.S. Department of State







The Honorable Earl W. Gast

Assistant Administrator
Bureau for Africa
U.S. Agency for International Development



Panel II

Berhanu Nega, Ph.D.

Associate Professor of Economics
Bucknell University

J. Peter Pham, Ph.D.

Director
Michael S. Ansari Africa Center
Atlantic Council








Mr. Obang Metho

Executive Director
Solidarity Movement for a New Ethiopia



Thursday 13 June 2013

TPLF accuses Blue Party on Day One

Blogging from her home in Oslo, Norway, activist Eden Abera says a day has hardly passed before TPLF accused the Blue Party of "issues" that the rally was called for in the first place. Here's her ViewPoint.
What is funny about TPLF's tactic is that after allowing the demonstration to be held so that it would deceptively make them look "democratic," they come back and accuse the opposition of all sorts of crimes.


The ruling party knows what kind of slogans the protesters would chant. Obviously, it is about political repression. The regime knows that protesters would call for the release of political prisoners and for the regime to stop interfering in religious affairs.
And here we go: The regime said on its own TV that the Blue Party is guilty of:
  1. Calling for the release of political prisoners which, it said, are accused of terrorism and their case is still pending court decisions.
  2. Defaming the regime as if the regime is interfering in the religious affairs.


Such charges were, no matter how funny they look, made by Communications Minister Shimelis Kemal who appeared on the same day on ETV, the mouthpiece of the regime. Shimelis said the government had taken corrective measures against evictions of farmers before the protesters took to the streets and shouted about it. He said this was nothing else but defaming his government. But it is widely known the forceful eviction is still continuing in different parts of Ethiopia.

Much to its credit, however, ETV reported one fact: The Blue Party has promised to return to the streets within three months. If they people rise up for their rights, TPLF knows it is the end of its brutal rule, and hence Shimelis Kemal's warning via ETV.

Thanks to technology, pictures and video clips of the protest rally were instantly beamed across Social Media networks and websites, despite TPLF's huge appetite to hide and bury the truth. TPLF cannot arrest the power of technology and the Ethiopian people's quest for democracy and justice. It is simply impossible.

Wednesday 5 June 2013

የግብፅ ፖለቲከኞች የጦርነት ቅስቀሳ በቀጥታ የቴለቪዥን ስርጭት ተጋለጠ





•    ‹‹የመንግሥት ተቃዋሚን በመደገፍ ማተራመስ ወይም ወታደራዊ ጥቃት›› ሲሉ መክረዋል
•    በግብፅ ተቀባይነት ያላቸው ተቃዋሚ ፓርቲዎች ውይይቱን አልተቀበሉትም

የኢትዮጵያ ታላቁ የህዳሴ ግድብ በግብፅና በሱዳን ላይ ሊያደርስ የሚችለውን ተፅዕኖ እንዲያጠና በሦስቱ አገሮችና ዓለም አቀፍ ባለሙያዎች የተቋቋመው ኮሚቴ በግድቡ ላይ ያቀረበውን ሪፖርት ተከትሎ፣ የግብፅ ፕሬዚዳንት መሐመድ ሙርሲ ከአገሪቱ ፖለቲከኞች ጋር ባደረጉት ውይይት፣ ፖለቲከኞቹ ኢትዮጵያን ለማተራመስ ካልሆነም በስውር ወታደራዊ ጥቃት ግድቡን ለመምታት መክረዋል፡፡
ነገር ግን ውጥናቸው በስህተት የቀጥታ ቴሌቪዥን ስርጭት ተጋልጧል፡፡ 

የቀጥታ የቴሌቪዥን ስርጭት ላይ ስለመሆናቸው የማያውቁት በፕሬዚዳንት ሙሐመድ ሙርሲ የተጋበዙት የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች የልባቸውን ካለመቆጠብ በመናገር፣ እንዴት ኢትዮጵያን ማጥቃትና በግብፅ ብሔራዊ ደህንነት ላይ አደጋ ጋርጧል በሚሉት ታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታን ማስተጓጐል እንደሚቻል ሐሳባቸውን ሰንዝረዋል፡፡ 


በውይይቱ ለተሳተፉት የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና የእምነት መሪዎች የአገሪቱ ፕሬዚዳንት መሐመድ ሙርሲ ንግግር በማድረግ ውይይቱ ተጀምሯል፡፡ ‹‹አንዲት ጠብታ የዓባይ ውኃ ልንተውላቸው አንፈቅድም፤›› በማለት ፕሬዚዳንቱ ባደረጉት ንግግር አቋማቸውን አስረግጠዋል፡፡ 

ይህንን የፕሬዚዳንቱን ንግግር ተከትሎ መድረኩ ለተሳታፊዎች ክፍት ሲሆን፣ የፖለቲካ አመራሮቹ በጉዳዩ ዙሪያ የግብፅን ጥቅም እንዴት ማስከበር እንደሚቻል ሐሳባቸውን ሰንዝረዋል፡፡ ‹‹ግብፅ የኢትዮጵያ መንግሥትን በትጥቅ ትግል እየተቃወሙ ያሉ የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎችን መደገፍ ይገባታል፤›› የሚል ሐሳብ ያቀረቡት ዩኒስ ማካዮን የተባሉ የአልትራኮንሰርቫቲቭ ኢዝላሚስት ፓርቲ መሪ ናቸው፡፡