Sunday 16 October 2016

Atronus, Tesfaye Tesemma, the journalist who challenged Jawar Mohammed, explains his thoughts part 1 and 2

Atronus, Tesfaye Tesemma, the journalist who challenged Jawar Mohammed, explains his thoughts part 1







Tuesday 4 October 2016

Friday 30 September 2016

ተቀምጠው የሰቀሉት


የኢራቅ ኩርዶች እንዲህ ይተርካሉ፤
አንዲት የልዑል ልጅ ነበረች፡፡ አንድ የምታፈቅረው ልጅም ነበረ፡፡ ታድያ ከአንድ የቤተ መንግሥቱ ጠባቂ ጋር ትመካከርና ይህንን ፍቅረኛዋን ክፍሏ ድረስ ታስገባው ነበር፡፡ የቤተ መንግሥቱ ጥበቃ የተወሰነ ገንዘብና ልብስ ትሰጠው ስለነበር በደስታ ምሥጢሩን ይደብቅ ነበር፡፡ አንድ ቀን ግን ያልታሰበ ነገር ተከሰተ፡፡ ልዕልቲቱና ፍቅረኛዋ አፕል ቆርጠው እየተጫወቱ ይበሉ ነበር፡፡ ሁለቱም አፋቸውን ከፍተው የአፕሉን ቁራጭ አንዳቸው ወደሌላቸው አፍ ወርውሮ የማስገባት ጨዋታ ነበር የሚጫወቱት፡፡ 
እየተሳሳቁ የአፕል ቁራጭ ወደየአፎቻቸው ሲወረውሩ ልዕልቲቱ የወረወረችው የአፕል ቁራጭ ድንገት የፍቅረኛዋ ጉሮሮ ውስጥ ተቀረቀረ፡፡ ውኃ ብትሰጠው፣ ማጅራቱን ብትመታው ሊወርድለት አልቻለም፡፡ ኡኡ ብላ እንዳትጮህ ልጁ ማነው? እንዴትስ መጣ ? ለሚለው ጥያቄ የምትመልሰው የላትም፡፡ በዚህ መካከል ልጁ ትንፋሽ አጥሮት ሞተ፡፡

የልጁ የመውጫ ሰዓት ሲደርስ የጥበቃ ሠራተኛው መጣ፡፡ እንደቀድሞው ግን ልጁን ደብቆ ሊያስወጣው አይችልም፡፡ አሁን ያለው ሬሳው ነው፡፡ ‹እባክህን የምትችለውን ሁሉ አድርገህ ይህንን ሬሳ አውጣልኝ፤ የምትፈልገውን ነገር ሁሉ አደርግልሃለው› አለቺው፡፡ የጥበቃ ሠራተኛውም ‹ምንም ችግር የለውም፤ የምፈልገው ግን ገንዘብ ወይም ልብስ አይደለም› አላት፡፡ እርሷም ‹ምንም ችግር የለም፡፡ ብቻ በቶሎ አውጣልኝ› ብላ ለመነችው፡፡ የጥበቃ ሠራተኛው ሬሳውን ቆሻሻ አስመስሎ ደብቆ  አወጣው፡፡ እርሷም እፎይ አለች፡፡
የጥበቃ ሠራተኛው ተመልሶ መጣና ቃል በገባችው መሠረት የሚፈልገውን ነገር እንድታደርግለት ጠየቃት፡፡ ‹ምን?› አለች ልዕልቲቱ፡፡ ‹ካንቺ ጋር መተኛት ነው የምፈልገው› አላት፡፡ ፀሐይ እንደበዛባት ቅል ክው አለች፡፡ ተናደደች፡፡ ‹ምን ደፋር ነህ ከልዕልት ጋር ለመተኛት የምታስብ፤ አሁን ከዚህ ጥፋ› አለቺው፡፡ እሺ ብሎ ወጣና የፍቅረኛዋን አስከሬን ይዞላት መጣ፡፡ ይኼኔ የምታደርገው ግራ ገባት፡፡ ያላት አማራጭ የሰውዬውን ፈቃድ ማሟላት ብቻ ሆነ፡፡ ተሸነፈች፡፡ በአንድ ቀንም ሦስት ነገሮችን አጣች፡፡ ፍቅረኛዋን፣ ክብሯንና የወደፊት ተስፋዋን፡፡ ፍቅረኛዋን በሞት፤ ክብሯንም በአገልጋይዋ እግር ሥር በመውደቅ፤ የወደፊቱንም ተስፋዋን ድንግልናዋን በማጣት፡፡ 
በዚህ ብቻ አላበቃችም፡፡ ያ የጥበቃ ሠራተኛ እየመጣ ‹አጋልጥሻለሁ› ይላታል፡፡ ያን ቀን ሬሳውን ይዞ የመጣበትን ጆንያም ያሳያታል፡፡ እርሷም ትፈራለች፡፡ በፍርሃትም የማትፈልገው ሰው እግር ሥር ትወድቃለች፡፡ ከእርሱም ጋር ትተኛለች፡፡ ይህ ግን ሊያዛልቃት አልቻለም፡፡ ባርነት ሰለቻት፡፡ ችግሮችን ለመጋፈጥ ካልፈለግህ ችግሮችን እያነገሥካቸው ትሄዳለህ› ይላሉ ኩርዶች፡፡ ችግርን ካታለልከው መልሶ ይይዝሃል፤ ከተጋፈጥከው ግን ጥሎህ ይሸሻል የሚል አባባልም አላቸው፡፡ 
ልዕልቲቱ አሁንም ችግሩን መፍታት ሳይሆን ማምለጥ ፈለገች፡፡ አንድ ሌሊት የጥበቃ ሠራተኛው ተደብቆ ወደእርሷ ሲመጣ ለአባቷ የምታዘጋጀውን የልዑሉን ወይን አሰናድታ ጠበቀቺው፡፡ በደስታ እየደጋገመ ጠጣ፡፡ ከእርሷም ጋር ከተኛ በኋላ እንደ ተሸነፈ ቦክሰኛ በድካም ተዘረረ፡፡ አርሷም እየጎተተች ወስዳ በልዑሉ መኝታ በር ላይ አጋደመችው፡፡ ሊነጋጋ ሲል ጠባቂዎቹ አዩት፡፡ ጠጋ ብለው ሲያሸቱት አፉ የወይን ጠጅ ይሸታል፡፡ የወይን ጠጁ ሽታ የልዑሉ ወይን መሆኑን ይመሰክራል፡፡ የልዑሉን ወይን ሰርቆ ጠጥቷል ብለው በአደባባይ ሰቅለው ገደሉት፡፡ ነገሩም በዚህ የተቋጨ መሰለ፡፡ ነገር ግን የዕብድ ቀን አይመሽም፡፡ ኩርዶች እንዲህ ይላሉ፡፡ የምትሠራው በር ምንጊዜም ልትሄድበት የምትችል መሆኑን አረጋግጥ፡፡ ለአንድ ጊዜ መውጫ ብለህ በሩን ከሠራኸው ከበሩ በኋላ ወዴት እንደምትሄድ ግራ ይገባሃል፡፡ በሩን ከነ መንገዱ አስበው፡፡ መንገዱን ከነ መዳረሻው፤ መዳረሻውንም ከነመቆያው፤ መቆያውን ከነ መክረሚያው፡፡ 
የጥበቃው ሠራተኛ በአደባባይ ሲሰቀል፤ የወይኑ ጣዕም አፉ ላይ ቀርቶ ስለነበር እየደጋገመ ከንፈሩን ይልስ ነበር፡፡ የዚህ ምክንያቱ የጠጣው የወይን ጠጅ ጣዕም ነው ተብሎ ተወራ፡፡ ይህንን ወሬ የሰማ የሌላ ልዑል ልጅም ይህንን ወይን ያዘጋጀቺውን የልዑሉን ልጅ ለማግባት ፈለገ፡፡ እናም ወደ ልዕልቲቱ አባት ሽማግሌዎች ላከ፡፡
ይህ ዜና ለአባቷ የምሥራች ለልዕልቲቱ ግን መርዶ ነበር፡፡ ድንግልናዋን አጥታለች፡፡ በኩርድ ደግሞ ድንግል ያልሆነቺውን ልጅ እንኳን ልዑላን ተራዎቹ ሰዎች አያገቡም፡፡ እስካሁን ችግሩን ከመጋፈጥ እየሸሸች፣ ነገር ግን አንዱን ችግር በሌላ ችግር እያለፈች መጥታለች፡፡ አሁን የመጋፈጫው ሰዓት ደረሰ፡፡ ችግርን በመፍትሔ መፍታትና ችግርን በሌላ ችግር ማለፍ ይለያያሉ፡፡ ችግርን በችግር ካለፍከፈው ጊዜ እየገዛህ ነው፡፡ ችግርን በመፍትሔ ካለፍከው ደግሞ ልብ እየገዛህ ነው፡፡ ይላሉ ኩርዶች፡፡ 
የልዕልቲቱ አባት ጋብቻውን መቀበሉን ስትሰማ እንደተለመደው ልዕልቲቱ አንድ ዘዴ ቀየሰች፡፡ አንዱን ታማኝ አገልጋይዋን ጠራችውና አንድ እፍኝ ወርቅ ሰጥታ እንዲህ ስትል አዘዘችው ‹በመላዋ ኢራቅ ዙር፡፡ በመልክም፣ በቁመትም፣ በጠባይም እኔን የምትመስል ልጅ ፈልገህ ለደንገጡርነት አምጣልኝ›፡፡ ሰውዬውም ለወራት ያህል ከቦታ ወደ ቦታ ዞረ፡፡ በመጨረሻም አንዲት ልጅ አገኘ፡፡ ልዕልቲቱ ስታያት ቁርጥ እርሷን ትመስላለች፡፡ እንዲህ አለቻት ልጅቱን፡፡ አሁን አንቺ ልዕልት ሆነሻል አሉ፡፡ የልዑሉንም ልጅ ታገቢያለሽ፡፡ የጫጉላውንም ጊዜ አብረሽው ታሳልፊያለሽ፡፡ እኔም ያንቺ ደንገጡር ሆኜ አንቺንና ልዑሉን ለጊዜው እታዘዛለሁ፡፡ ልክ የጫጉላው ጊዜ እንዳለፈ ግን ትቀይሪኛለሽ፡፤ እንቺ ወደ ደንገጡርነትሽ እኔም ወደ እመቤትነቴ እመለሳለሁ፡፡ ለዚህ ውለታሽም ለጥሎሽ የሚመጣውን ሀብት ሁሉ ትወስጃለሽ› አለቻት፡፡ ልጂቱም በደስታ ተፍነከነከች፡፡ 
የሠርጉ ቀን ደረሰ፡፡ ደንገጡሯዋ የሙሽራ ልብስ ለበሰች፡፡ እመቤቲቱ ደግሞ የአገልጋይ ልብስ ለበሰች፡፡ ማንም ሊለያቸው የቻለ የለም፡፡ ልዑሉ መጣ፡፡ ሙሽራዋን ይዞ ሄደ፡፡ አገልጋይዋም ተከትላ ሄደች፡፡ በልዑሉ ቤት የነበረው ድግስ ሲያልቅ ልዑሉና ሙሽራዋ ወደ ጫጉላ ቤት ገቡ፡፡ አገልጋይዋም ከውጭ ቀረች፡፡ ታስበዋለች፡፡ ይህ ዕድል የእርሷ ነበር፡፡ ነገር ግን አሁን አይደለም፡፡ አሁን እርሷ ነበረች እዚያ ውስጥ መሆን የነበረባት፤ ግን ችግርን ለማለፍ ብላ በፈጠረችው ችግር ምክንያት ውጭ ቆማለች፡፡ እዚህ ደረጃ ሳትደርስ ነገሮችን አስተካክላ በክብር ልትወጣ ትችል የነበረባቸውን ዕድሎች ታስታውሳለች፡፡ ዕድሎች ሁሉ አምልጠዋታል፡፡ ችግሮችን በሌላ ችግር በመተካት ዕድሎችን አምክናቸዋለች፡፡ ስለዚህም ክብሯን ለሌላዋ አሳልፋ ሰጠቻት፡፡ ሕዝቡ ጫጉላ ቤት ያለቺው እርሷ መስላቸዋለች፡፡ ግን አይደለችም፡፡ የተመረጠችው እርሷ፣ ወደ ሠገነት የወጣችው ሌላዋ፡፡ የተዳረችው እርሷ፣ ያገባችው ሌላዋ፡፡
የጫጉላዎቹ ቀናት አለፉ፡፡ ልጂቱ ግን ወደ አገልጋይነቷ ልትመለስ አልቻለችም፡፡ አንድ ቀን መታጠቢያ ቤት ውስጥ እመቤትና ደንገጡር ተገናኙ፡፡ ደንገጡሯም ‹አሁን በቃሽ ወደቦታሽ ተመለሽ፡፡ ለውለታሽ ያዘጋጀሁትን ስጦታሽን ውሰጅ; አለቻት፡፡ እመቤቲቱም ‹የዋሕ ነሽ፡፡ ላየው የማልችለውን አሳየሺኝ፤ ላገኘው የማልችለውን ሰጠሽኝ፤ ልደርስበት የማልችለው ቦታ አደረሽኝ፡፡ ያኔ እሺ ስልሽ ይህንን ሁሉ አላውቅም ነበር፡፡ አልጋው እንዲህ የሚመች መሆኑን አልቀመስኩም ነበር፡፡ ክብሩ እንዲህ የሚያጓጓ መሆኑን አላውቅም ነበር፡፡ ምቾቱ እንዲህ ልብ የሚለሰልብ መሆኑን አላውቅም ነበር፡፡ ላንቺ ከደንገጡርነት ወደ እመቤትነት መምጣት ቀላል ይሆናል፡፡ ለእኔ ግን ከእመቤትነት ወደ ደንገጡርነት መውረድ ከባድ ነው፡፡ ይህንን የመሰለ ነገር ከቀመስኩ በኋላ ትተውልኛለች ብለሽ ማሰብሽ ሞኝነትሽ ነው፡፡ አልጋ አንዲህ በቀላሉ የሚተው አይደለም፡፡ ሀብቱ ሁሉ የእኔ መሆኑን እያየሁ ያንቺ ስጦታ የሚያጓጓኝ ይመስልሻል› አለቻት፡፡ 
›እነሆ› ይላሉ ኩርዶች፡፡ እነሆ በዚህ የተነሣ አገልጋይቱ እመቤት፣ እመቤቲቱም አገልጋይ ሆነው ኖሩ፡፡ ተቀምጣ የሰቀለቺውን ቆማ ማውረድ አቅቷት፡፡ 
ኤድመንተን፣ ካናዳ

Wednesday 28 September 2016

የተካደ ትውልድ (በ.ሥ)


የተካደ ትውልድ
አይዞህ ባይ የሌለው
ታዳጊ የሌለው
ወይ ጠባቂ መላክ፤ ወይ አበጀ በለው
ደርሶ ከቀንበሩ የማይገላግለው
የተካደ ትውልድ ፤
አብዝቶ የጾመ፤ ተግቶ የጸለየ
ጥቂት መና ሳይሆን፤ ጥይት ሲዘንብ ያየ
እድሜ ይፍታህ ተብሎ ፤ የተወለደ’ ለት
አምባሩ ካቴና፤ ማተቡ ሠንሠለት፡፡
ምቾትን የማያውቅ ፤ ረፍት የተቀማ
አልጋው ያጋም እሾህ፤ ምኝታው የሣማ
የተካደ ትውልድ፤
ሞቶ እንኳ ሬሳው፤ አይላላለት ቀንበር
በዘብ እጅ ተገድሎ፤ በሹም የሚቀበር
ከጡት አስጥል በላይ፤ ኑሮ የመረረው
እንዳይሄድ፤ ጎዳናው፤ የተደናገረው
ድል ያልሰመረለት ትግል ሳይቸግረው
የተካደ ትውልድ
በሥጋ በነፍሱ
በቀልቡ በገላው
ኧረ ምንድን ይሆን ፤ ምንድን ይሆን መላው?

Thursday 25 August 2016

መሳደብ ተሸናፊነት እንጅ አሸናፊነት አይደለም

ከዕለታት በአንዱ ቀን በአንዲት ሀገር በሚገኝ አንድ መካነ ትምህርት (ዩኒቨርሲቲ) ውስጥ በሥነ-ልቦና (ሳይኮሎጂ) የትምህርት ዘርፍ በአንደኛው ክፍለ ጊዜ የሚያስተምሩ አንድ መምህር ለተማሪዎቻቸው ይህንን ጥያቄ አነሱ፡- ‹‹ሰዎች ለምን ይሳደባሉ?›› የሚለውን፡፡ ተማሪዎችም የመሰላቸውንና በአዕምሯቸው ለስድብ ምክንያት ይሆናል ብለው ያሰቡትን/የገመቱትን ሁሉ መናገር ጀመሩ፡፡ 

 አንደኛው ተማሪ፡- ‹‹በእኔ ግምት ሰዎች ሰዎችን የሚሳደቡት ስለሚበሳጩና ተሰዳቢዎችንም ለማበሳጨት ሲሉ ነው፡፡››
መምህሩ፡- ‹‹ሰዎች በሰዎች ለምን ይበሳጫሉ? ሰዎችንስ ለማበሳጨት ለምን ይፈልጋሉ?››
ተማሪው፡- ‹‹ምን አልባት ስለሚጠሏቸው ይሆናል፡፡››
መምህሩ፡- ‹‹ሰው ሰውን ለምን ይጠላዋል? … ተማሪው ግራ ተጋብቶ ዝም አለ፡፡
ሁለተኛው ተማሪ፡- ‹‹እኔ ደግሞ ሰዎች ሰዎችን የሚሳደቡበት ዋናው ምክንያት ከሀሳባቸው በመነሳት ማለትም የሚናገሩት ንግግር ስለሚያናድዳቸው ይመስለኛል፡፡ አንዳንድ ሰዎች የሚያስቡት ሀሳብና የሚናገሩት ንግግር በጣም ያናድዳል፡፡ እነዚያ አናዳጅ ሰዎች ካልተሰደቡ ሊስተካከሉ አይችሉም፡፡››
መምህሩ፡- ‹‹በሰዎች ሀሳብ መናደድ ስትል… የሰዎችን የአዕምሮ ሀሳብ ማወቅ ይቻላልን? ያልተነገሩ/ያልተገለጹ ሀሳቦች ሊያናድዱ የሚችሉበት መንገድ ሊኖር ይችላል? የሰዎች ንግግርስ ለምን ያናድደናል? መልካም ያልሆኑ ንግግሮች ቢኖሩስ በስድብ ነው ማስተካከል የምንችለው?›› … ይህኛው ተማሪም መልስ አጥቶ ዝም አለ፡፡
ሦስተኛው ተማሪ፡- ‹‹በእኔ በኩል… ሰዎች ሰዎችን የሚሳደቡት እንዲሁ በአዕምሮ ከሚፈጠር ጥላቻ የተነሳ ይመስለኛል፡፡ አለ አይደል… አንዳንድ ሰዎች እንዲሁ ይደብራሉ… በቃ የሆነ ስደባቸው ስደባቸው የሚልህ ስሜት ይመጣብሃል፡፡ ያኔ ትሳደባለህ፡፡››
መምህሩ፡- ‹‹በመሠረቱ ሰውን እንዲሁ መጥላት ትክክል ነው ትላለህ? ‹ሰው ዝም ብሎ ይደብራል› ያልኸው ንግግርህ ራሱ ይደብራል፡፡ ከእነርሱ በኩል ምንም ቃል ሳይወጣ ሀሳባቸውን ሳታውቅ እንዴት ስታያቸው ብቻ ስደባቸው ስደባቸው ሊልህ ይችላል?››
መምህሩ ከዚህ በላይ ለተማሪዎች የመገመት ዕድል መስጠት አልፈለገም፡፡ በሦስተኛው ተማሪ ግምት ቢናደድም ራሱን አረጋግቶ ገለጻ ማድረጉን ቀጠለ፡፡

‹‹ተማሪዎች… አንድ ማስተዋል ያለባችሁ መሠረታዊ ነገር አለ፡፡ ይኸውም የስድብ መነሻው የተሳዳቢው ልብ/አዕምሮ እንጅ ተሰዳቢው አለመሆኑን ነው፡፡ ሰዎችን የምንሰድባቸው በአዕምሯችን ለእነርሱ ከሰጠነው ሥዕል በመነሳት እንጅ እነርሱ በትክክል ለመሰደብ የሚያበቃ ችግር ስላለባቸው አይደለም፡፡ ሰዎች በምንም መልኩ ስህተት ቢሠሩ እንኳን በመሳደብ ከስህተታቸው ልናርማቸው አንችልም፡፡ እንዲያውም ለበለጠ ጥፋት ነው የምናዘጋጃቸው፡፡ ለመሰደብ ብሎ ክፉ ነገር የሚሠራ ሰውም አይኖርም፡፡ ስህተቱን ሊፈጽመው የሚችለው ባለማስተዋል/ባለማወቅ ነው፡፡ ያንን ስህተት ልናስተካክለው የምንችለው ደግሞ በማስተማር ብቻ ነው፡፡ 

 በሌላ በኩል ደግሞ ሰዎች ትክክል አይደሉም በሎ ማመን በራሱ ስህተት ነው፡፡ ስህተት ናቸው ብለን ያመነው ከእኛ ምልከታ አንጻር እንጅ ነገሩ በትክክል ስህተት ሆኖ ላይሆን ይችላል፡፡ በመሠረቱ ‹ፍጹም ስህተት የሆነም ፍጹም ትክክል የሆነም ሀሳብ የለም›፡፡ ሁሉም ነገር አንጻራዊ ነው፡፡ ሰዎች ሁሉ ለነገሮች ያላቸው ምልከታና ግንዛቤ ይለያያል፡፡ ‹የግድ እንደኔ ካልተመለከትኸው ስህተት ነህ› ማለት ጤነኛ አስተሳሰብ አይደለም፡፡ በተለይም ለስድብ መሮጥ የአለማወቅን ጥግ ነው የሚያሳየው፡፡ ነገሩን በተሳሳተ መንገድ የተረዳነው እኛው ተሳዳቢዎች ብንሆንስ? የእኛን ትክክለኛነት እንዴት አረጋገጥን? የእነርሱን ስህተትነትስ? ስህተትነታቸውን ብናረጋጥስ መሳደባችን የእነርሱ ችግር ሊሆን ይችላልን? በፍጹም፡፡ ስድብ የተሳዳቢው እንጅ የተሰዳቢው ችግር አይደለም፡፡

 ከእያንዳንዱ ስድብ ጀርባ የተሳዳቢው ድክመት አለ፡፡ ተሳዳቢው የመሳደቡ ምሥጢር የተሳደበበት ነገር ለራሱ ሰላም ስለነሳው ወይም ስላበሳጨው ሊሆን ይችላል፡፡ ነገር ግን አንድ ሰው በነገሮች ሁሉ ሰላም የሚያጣና የሚበሳጭ ከሆነ በራስ የመተማመን ችግር እንዳለበት በግልጽ ያሳያል፡፡ የሌሎች ሀሳብ የሚረብሸው ሰው ሀሳብን በሀሳብ ማሸነፍ የማይችል ደካማ ሲሆን ነው፡፡ ባጭሩ ‹መሳደብ ተሸናፊነትን እንጅ አሸናፊነትን አያሳይም›፡፡ የሚያሸንፍ ሁሉ በአሸናፊነቱ ደስ ይለዋል እንጅ አይናደድም አይሳደብምም፡፡
ሰዎች እንዲሁ የሚደብሩንና የምንጠላቸው ከሆነ ደግሞ በውስጣችን ያለው ፍቅር እንደተሟጠጠና ልባችን በጥላቻ መንፈስ እንደተሞላ ያሳያል፡፡ እንዴት ሰው ዝም ብሎ ይደብራል ይባልል? እንኳን ሰው ምንም ነገር የሚያስጠላን ከሆነ ችግሩ ያለው ከእኛው ጋር ነው፡፡ ‹ጥላቻ የሚመነጨው ከውስጣችን እንጅ ከውጭ አይደለምና›፡፡ እኛ የጠላንበት ምክንያት የአዕምሯችን ስሌት እንጅ የነገሮች ሐቂቃ አይደለም፡፡ የሰው ልጅ ልቡ ከፍቅር ሲራቆት የሆነ ያልሆነውን ምክንያት እየፈጠረ ነገሮችን መጥላት ይጀምራል፡፡ ምክንያት ፈልጎ መውደድ እንጅ ምክንያት ፈልጎ መጥላት ለሰው ልጅ የሚጠቅም ባሕርይ አይደለም፡፡ ከሁሉም ሰው ዘንድ መልካም ነገር አለ፡፡ ነገር ግን የእኛ እይታ በጥላቻ ከተሸፈነ ያንን መልካም ነገር ልናገኘው አንችልም፡፡ 

 በሌላ በኩል መሳደብ ትዕግሥት የሌላቸውና ነገሮችን የማመዛዘን አቅምን ያላዳበሩ ሰዎች ምልክት ተደርጎም ይወሰዳል፡፡ ለበጎም ሆነ ለመጥፎ ነገሮች ምላሽ ከመስጠት በፊት በትዕግሥት አመዛዝኖ ማየት መልካም ነው፡፡ አዕምሯዊ ሆነን የመፈጠራችን ምሥጢርም እንድናመዛዛን ነው፡፡ የሰው ልጅ በስሜት ብቻ ይነዳ ዘንድ መልካም አይደለምና፡፡
ሰበብ እየፈለጉ ከአንደበታቸው ስድብን ብቻ የሚያወጡ ሰዎችም አሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች ካልተሳደቡ ሰላም የማይሰማቸው አይነቶች ናቸው፡፡ ይህ የሥነ-ልቦና (ሳይኮሎጂ) ችግር ነው፡፡ መታከም ያለበት በሽታም ነው፡፡ ጤነኛ ሰው ለመሳደብ አይፈጥንም፤ በመሳደብም አይኖርም፡፡ ሰዎች ካልተሳደቡ የሚያማቸው ከሆነ በሽታው የመሳደብ ልምዳቸው ነው፡፡ ከስድብ ሱሳቸው እስካልተላቀቁ ድረስም በሽተኛ ሆነው ይቀጥላሉ፡፡ ተሳዳቢነት በምንም መስፈርት ጤነኝነትሊሆን አይችልም፡፡ ልንታከመው የሚገባ ትልቅ በሽታ እንጅ፡፡››
ተማሪዎች በጸጥታ ውስጥ ናቸው፡፡ መምህሩ ዝም ሲል ሁሉም ጭንቅላታቸውን በአዎንታ ነቀነቁ፡፡ በፊታቸው ላይ የሚታየው የመገረም ስሜትም በግልጽ ይነበብ ነበር፡፡ ውስጣቸው በአንዳች የጥበብ እሳት ሲቃጠል የእሳቱ ነበልባልም ልባቸውን ሲገርፈው ብርሃኑ በፊታቸው ላይ ተንፀባርቆ ይታይ ነበር፡፡ ማንኛቸውም እንደዚህ አስበውት አያውቁም ነበርና በአዲስ እይታ ውስጥ ለአዳዲስ ሀሳቦች መብረር የጀመረው አዕምሯቸው የሰሙትን ከማድነቅ ሌላ አማራጭ አልነበረውም፡፡ በስሜት የምትለፈልፍ ምላሳቸውም በልባቸው የመገረም ልጓም ተገትታ ዝምምም አለች፡፡

‹‹ግልጽ ያልሆነና እንዲብራራላችሁ የምትፈልጉት ሀሳብ ካለ አንሱና እንነጋገር፡፡ ተጨማሪ ማብራሪያ ያለውም አይከለከልም…›› አሉ መምህሩ በጸጥታ ውስጥ ከተቀመጡት ተማሪዎቻቸው ፊት ለፊት እንደቆሙ፡፡ አሁንም ዝምታ ሰፈነ፡፡ ሁሉም ከዚህ ክፍለ ጊዜ በፊት ስለ ስድብ የነበረውን ግምትና ግንዛቤ ከመምህሩ ገለጻ ጋር እያነጻጸረ በመገረም ላይ ነው፡፡
በመጨረሻም አንድ በዕድሜ ሸምገል ያሉ ተማሪ (በዕድሜ ለአንቱታ የደረሱ) እጃቸውን አነሱና ተፈቅዶላቸው ተናገሩ፡፡ ‹‹… መምህራችን ያሉት ሁሉ እውነታ ያለውና ልንማርበትም ልናስተምርበትም የሚገባ ታላቅ ቁምነገር ነው፡፡ ነገር ግን እስካሁን ያልተተቀሰ የስድብ ዐቢይ ምክንያትም አለ፡፡ ይኸውም የክፉ መናፍስት ድር ነው፡፡ ሰዎች ተሳዳቢ የሚሆኑት ከክፉ መንፈስ የተነሳም ሊሆን ይችላል፡፡ ክፉ መንፈስ በሰዎች ላይ እያደረ ተሳዳቢ ያደርጋቸዋል፡፡ መሳደባቸውን እንደ ጽድቅ የሚቆጥሩና ብልግናቸውን እንደ ጀብዶ የሚያወሩ ሰዎች የመብዛታቸው ምስጢርም ከራሳቸው የሥነ-ልቦና ድክመት በተጨማሪ የክፉ መናፍስት ተሸካሚ መሆናቸውም ጭምር መሆኑ መዘንጋት የለበትም፡፡ በቅዱሱ መጽሐፍ በዮሐንስ ራእይ በምዕራፍ 13 ላይ የተጻፈውን ማንበብም ለተናገርሁት ማስረጃ ነው፡፡ ‹… አውሬውን ማን ይመስለዋል፥ እርሱንስ ሊዋጋ ማን ይችላል? … ታላቅንም ነገርና ስድብን የሚናገርበት አፍ ተሰጥቶታልና…› ይላል ቃሉ፡፡ እንግዲህ በቅዱስ መጽሐፍ አምናለሁ ለቃሉም እገዛለሁ የሚል ሰው አፉ እንዳመጣለት የሚሳደብ ከሆነ ለአውሬው የነፃ ፈቃድ አግልግሎት እየሰጠ ነው ማለት ነው፡፡ አውሬው ስድብን ብቻ ሳይሆን ታላቅ ነገርንም እንደሚናገር እናስተውል፡፡ ታላቅ ነገርን የሚናገሩ ሁሉ ቢሳደቡም አይግረመን፡፡ አንዳች ክፉ መንፈስ ካልለከፈው በቀር ሰውን ያህል ክቡር ፍጡር አፉን ለስድብ አይከፍትም፡፡ መሳደብ በሁሉም ዘንድ የተነቀፈና ከሰውነት ተራ የሚያስወጣ ነውረኛ ተግባር ነውና ሁላችንም ከመሳደብ እንታረም፡፡››
መምህሩም ተማሪዎችም በሌላ የመገረም ስሜት ዝም አሉ፡፡ ክፍለ ጊዜውም አበቃ፡፡ መምህሩም ለተማሪዎች የቤት ሥራ ሰጥተዋቸው ወጡ፡፡ የቤት ሥራውም እንዲህ የሚል ነው፡-
‹‹ሰዎች ምንም ይሁኑ ምን በፍጹም መሳደብ እንደሌለብን የሚያስገነዝቡ ቢያንስ 5 ምክንያቶችን ከሥነ-ልቦናም ሆነ ከሌላ አስተምህሮ አንጻር ጽፋችሁ ኑ፡፡››

Source Diretube

Sunday 7 August 2016

US First Daughter Sasha Obama serves seafood in summer job

Sasha Obama, daughter of US President Barack Obama, has swapped the comforts of the White House for the counter of a seafood restaurant, US media report.
The 15-year-old has taken a summer job serving food at the business in Martha's Vineyard, Massachusetts.
Sasha, using her full name, Natasha, has been accompanied to the restaurant by a contingent of six secret service agents, the Boston Herald reports.
The town has been a favourite location for the Obamas on their summer breaks.
Photographs show the president's youngest daughter wearing the restaurant's uniform of blue T-shirt and cap and working at a till.
A co-worker told the Herald: "She's been working downstairs at takeout. We were wondering why there were six people helping this girl, but then we found out who it was."
The White House has not commented on the report but First Lady Michelle Obama has spoken about trying to bring her two daughters up as normally as possible.
As well as working on the takeaway counter, Sasha Obama's other duties reportedly include waiting on tables and helping to prepare the restaurant for its lunchtime opening.
Her security team has been seen waiting nearby in a large car or sitting on benches while the First Daughter deals with tourists' meals.
Image result for obama daughter workingImage result for obama daughter workingImage result for obama daughter working

Tuesday 26 July 2016

መንግስት ተዝረከረከ፤ ወገኛ ‹ህዝብ› በዛ፤ አገር በግጭት ተመሳቀለ፤ ‹የአፍሪካ መዲና› በቆሻሻ ሽታ ታወደ


ሰዎች፣ “የዘራነውን እያጨድን ነው”

   አዲስ አበባ ለወትሮም ከቆሻሻና ከመጥፎ ሽታ፣ ትንሽ እፎይታ የሚያስብል ትንሽ ፋታ ያገኘችበት ጊዜ የለም፡፡ የክረምት ዝናብ ሲመጣ፣ አገስ ገሰሱን ጠራርጎ የሚያፀዳ ከመሰላችሁ ተሳስታችኋል፡፡ ዝናብ ሲያባራ፣ በየጎዳናው የምታዩት ጎርፍ፣ ጥቁረቱ ያስፈራል፡፡ ሽታው ያጥወለውላል፡፡ በየመፀዳጃ ቤቱና በየቱቦው የተጠራቀመውን ቆሻሻ ጎልጉሎ፣ በየአደባባዩ ይዘረግፈዋል፡፡ 

የቆሻሻ ሽታ በከተማዋ የተባባሰው ግን፣ ባለፉት አምስት አመታት ነው፡፡ ድሮ ድሮ፣ በየቦታው ከሚከማቸው ቆሻሻ፣ ግማሽ ያህሉ በመኪና እየተጫነ ይወሰድ ነበር፡፡ ግማሹ ደግሞ፣ እዚያው እየበሰበሰ ከተማዋን በሚሰነፍጥ መጥፎ ሽታ ያውዳታል። ብዙ ሰው ይህንን የማማረር ልምድ ነበረው፡፡ መንግስትም፣ ቆሻሻውን ሙሉ ለሙሉ ለማንሳትና ለማፅዳት ቃል ከመግባት አይቦዝንም ነበር - “ሁሉም ሰው አካባቢውን ቢያፀዳ፣ ከተማዋ ትፀዳለች” የሚል ማምለጫ መፈክርንም እየተጠቀመ፡፡ 

ካለፉት አምስት ዓመታት ወዲህ ግን፣ አዲስ ፈሊጥ መጥቷል - “ቆሻሻ ሀብት ነው”  የሚል ፈሊጥ። ይሄ ቀልድ አይደለም፡፡ የከተማዋ መስተዳድር፣ ይህንን ፈሊጥ በደማቁ እያተመ በየአካባቢው ሲለጥፍ አይተናል፡፡ ከዚህም ጋር፣ “ቆሻሻን መልሶ መጠቀም” የሚል ስብከት፣ የእለት ተእለት ድግምት ሆኗል። ከዚህ በኋላ ነው፤ በየሰፈሩ ቆሻሻ እያጠራቀሙ መከመር፣ እንደ ቁም ነገር መታየት የተጀመረው፡፡ በቃ፤ ፋታ የሌለው መጥፎ ሽታ፣ የከተማዋ የዘወትር ድባብ ሆነ፡፡ 

ቆሻሻው የሚነሳው፣ እንደ ተራራ ከተከመረ በኋላ ነዋ፡፡ ካለፈው ሳምንት ወዲህ ደግሞ፤ ተከምሮ ተከምሮ እዚያው እየበሰበሰ ነው፡፡ ከከተማዋ ውጭ የሚገኘው ቆሻሻ መጣያ ድንገት ተዘግቷል፡፡ በቃ፣ ከዳር ዳር፣ ቀን ከሌት፣ ክፉኛ የምትሰነፍጥ ከተማ ሆናለች  አዲስ አበባ፡፡
በሌሎች የአገሪቱ ከተሞች ፈፅሞ ያልታየ ሰፊ የኮሌራ ወረርሽኝ በአዲስ አበባ መከሰቱ ምን ይገርማል?
ብዙ መመራመር አያስፈልግም፡፡ መንግስት በጣም ከመዝረክረኩ ተነሳ፣ ከተማዋ በቆሻሻ ተጥለቅልቃ፣ ውሎና አዳሯ ከመጥፎ ሽታ ጋር ሆኗል። ነገር ግን ብዙዎቻችንም፣ የዚህ ጥፋት ተካፋዮች መሆናችንን ማስተዋል አለብን፡፡ “ቆሻሻ ሀብት ነው” የሚለው ፈሊጥ፣ ውሎ አድሮ ከተማዋን ለቆሻሻ ክምር፣ ነዋሪዎቿን ለኮሌራ ወረርሽኝ እንደሚዳርግ ማወቅና መናገር ነበረብን፡፡ ግን፣ የተናገረ አለ? ይሄ ቀልድና ጨዋታ ይቅርብን ብሎ ምክር የለገሰ ሰውስ አለ? “ቆሻሻን መልሶ መጠቀም” በማለት፣ የአካባቢ ጥበቃ ቡድኖች፣ ጋዜጠኞች፣ ምሁራንና ባለስልጣናት ስብከታቸውን ለአመታት ሲያዘንቡብን፣ “ኧረ ለንፅህና ቅድሚያ እንስጥ” ብሎ የተከራከረ ሰው ካለ ንገሩኝ፡፡ 

“ግንኮ ቆሻሻን መልሶ መጠቀም ይቻላል፡፡ ጥሩ ነው፡፡ መልሶ መጠቀም ከተቻለ ደግሞ ቆሻሻ ሀብት ይሆናል” ብሎ ዛሬም የሚከራከር ይኖራል፡፡ ይሄ ዝርክርክ አስተሳሰብ ነው፡፡ ከመነሻው አንድ ነገር፤ የማንጠቀምበትና የሚጎዳ ሲሆን ነው ቆሻሻ ተብሎ ከየቤቱ የሚወጣው፡፡ አለበለዚያማ አውጥተን ለምን እንጥለዋለን? ከጣልነውም፣ ተሻምቶ የሚወስድ አይጠፋም ነበር፡፡ በቃ፣ ቆሻሻ ነው፡፡ የንፅህና ጉድለት መጥፎ መሆኑንና ቆሻሻን ማፅዳት እንደሚያስፈልግስ አናውቅም? በአጭሩ፣ ቆሻሻን ማስወገድ ቀዳሚ ትኩረት መሆን ነበረበት - ስለ ቆሻሻ የምናስብ ከሆነ። ምናልባት፣ የተወሰነውን ቆሻሻ መልሶ መጠቀም የሚችል ሰው ካለ … ይቅናው፡፡ ዋናው ቁም ነገራችን ግን፣ ቆሻሻን ማስወገድና ማፅዳት መሆን ነበረበት፡፡  እንዲህ በእውነታ ላይ ተመስርተን በስርዓት ማሰብ ብንችል ኖሮ፣ “ቆሻሻ ሀብት ነው” በሚል ፈሊጥ አብረን ከመጨፈር ወይም በዝምታ ከማለፍ ይልቅ፣ መንግስት ወደ ህሊና እንዲመለስ መምከር እንችል ነበር፡፡ ምን ለማለት ፈልጌ ነው? በዝርክርክ አስተሳሰብ፣ “ቆሻሻ ሀብት ነው” የሚለውን ፈሊጥ እንደ ዋና የኑሮ መርህ የምንሰብክ፣ የምንቀበል አልያም በቸልታ የምናስተናግድ ከሆነ ግን፤ ተያይዘን የቆሻሻ ክምር ስር ተጨፍልቀን ለማደር እንደተስማማን ይቆጠራል፡፡ 

ዝርክርክ አስተሳሰብና ጭፍን ሃሳቦች፣ በተግባር መዘዝ እንደሚያስከትሉ ማወቅ አለብን፡፡ ጭፍን ሃሳቦችን እየሰበክን፣ እየተቀበልን ወይም በቸልታ እያስተናገድን የከረምን ሰዎች፤ ውሎ አድሮ መዘዙ ሲመዘምዘን፣ በቆሻሻ ሽታ እና በኮሌራ ስንወረር፣ … መንግስትን ለማማረርና ባለስልጣናትን ለመውቀስ እንሯሯለጣለን፡፡ ይሄ፣ … ወገኛ ግብዝነት ነው፡፡ 

ሌሎቹንም ችግሮች ተመልክቷቸው፡፡ ከ20 ዓመት በፊት፣ እነ ኢህአዴግ፣ ኦነግ፣ መአህድ እና የመሳሰሉ ፓርቲዎች ነበሩ የብሄር ብሄረሰብ ፖለቲካ ፊታውራሪዎች፡፡ ዛሬ ግን፤ ብዙ ሰዎች ወደ ጭፈራው ተቀላቅለዋል፡፡ ሌሎቻችን ደግሞ አብረናቸው ባንጨፍርም፣ በዝምታ ከማስተናገድ ያለፈ ቁም ነገር እየሰራን አይደለም፡፡ 

ታዲያ፣ በዘረኝነት የተቃኙና በብሄረሰብ የተቧደኑ ግጭቶች በየቦታው ሲቀጣጠሉ፣ ተጠያቂው ማን ነው?  አዎ፣ መንግስት ትክክለኛ ኃላፊነቱን ስላልተወጣ ጥፋተኛ ነው፡፡ በብሄረሰብ ተቧድነው ግጭት የሚቆሰቁሱ ሰዎችም፣ ዋና ጥፋተኞች ናቸው። ነገር ግን፣ ዘረኝነትን እንዲሁም የብሄር ብሄረሰብ ፖለቲካን፣ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የሚያስተጋቡ ብዙ ሰዎችም፣ ጥፋተኞች ናቸው፡፡ በቸልታ ዝምታን የመረጥን ሰዎችም፣ ከጥፋት የፀዳን አይደለንም፡፡ 

እናም፤ ግጭት በተፈጠረ ቁጥር መንግስትንና ባለስልጣናትን ብቻ ማውገዝ፣ ቀሽም ግብዝነት እንዳይሆንብን፣ የብሄር ብሄረሰብ ፖለቲካንና የዘረኝነት አስተሳሰብን ከስረ መሰረቱ መቃወም ይኖርብናል፡፡ በጅምላ የመፈረጅና የመናገር በሽታችንን ማስወገድ አለብን፡፡ እያንዳንዱን ሰው፣ በስራውና በባህርይው የምንመዝንበት ስልጡን አስተሳሰብ ይዘን ጥረት ካላደረግን፣ ወገኛ ሆነን እንቀራለን፡፡ 
 
ይህን ብቻ አይደለም፡፡
ኢንቨስትመንትንና ባለሀብትን በጭፍን በመጥላት በኩል፤ የ60ዎቹ ዓመተ ምህረት ሶሻሊስት ምሁራን፣ ኢህአፓንና ኢህአዴግን ጨምሮ በርካታ የአገራችን ፓርቲዎች በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ፡፡ ነገር ግን፣ ስንቶቻችን ነን፣ የሀብት ፈጠራ ስኬታማነትን እንደ ጀግንነት የምንቆጥረው? በኢቲቪ የሚሰራጨው “ማያ” የተሰኘውን አሰልቺ ፕሮግራም ለአፍታ ተመልከቱ፡፡ የግል ሆስፒታሎችንና ክሊኒኮችን የሚያወግዝ ተከታታይ ፕሮግራም፤ ከዚያ ደግሞ የግል ትምህርት ቤቶችን በዘመቻ ለመዝጋት የሚቀሰቅስ ፕሮግራም፤ በዚህ ሳምንት ደግሞ በደፈናው ባለ ሀብቶችን የሚያወግዝ ፕሮግራም … 

“ማያ” የሚያሰራጫቸው፣ እንዲህ ዓይነት ሃሳቦች ለአገራችን አዲስ አይደሉም፡፡ ከአገራችን ባህል ጋር የተሳሰሩ ነባር ሃሳቦች ናቸው፡፡ ከአገራችን ፓርቲዎችና ከፖለቲከኞች፣ ከጋዜጠኞችና ከምሁራን ዘወትር የምንሰማው ተደጋጋሚ ስብከት ምን ሆነና! በዚህ ስብከትም ነው፤ መንግስት በየጊዜው፣ በዋጋ ቁጥጥርና በአላስፈላጊ ገደቦች፣ የግል ኢንቨስትመንትን  የሚያዳክሙ ተግባራት የሚፈፀመው፡፡ በዚህ ስብከትም ነው፣ መንግስት በየመስኩ በቢዝነስ ስራ ላይ ለመሰማራት ከፍተኛ ሀብት የሚያባክነው፡፡ 
በአንድ በኩል፣ ሚኒባስ ታክሲዎች በኪራሳ ከገበያ እየወጡ የሚገኙት በአላስፈላጊ የመንግስት ቁጥጥር ሳቢያ ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ፤ መንግስት ለአዲስ አበባ ካመጣቸው ባቡሮች መካከል ግማሾቹ በብልሽት ያለ አገልግሎት መቀመጣቸውን ተመልከቱ። ታዲያ፤ ‹‹በትራንስፖርት እጥረት ተንገላታን›› በማለት መንግስትን ተጠያቂ ብናደርግ ይገርማል? አይገርምም፡፡ ነገር ግን፤ የሃብት ፈጠራ ስኬታማነትን የማናከብር ከሆነ፤ በተቃራኒው መንግስት በቢዝነስ ስራ ላይ መሰማራቱን የምንደግፍ ከሆነ፤ እኛም የጥፋቱ ተካፋይ ነን፡፡ 
ሰዎች ራሳችንን ባናታልልና ባንሞኝ ይሻላል፡፡ የዘራነውን ነው እያጨድን ያለነው፡፡