Sunday, 12 July 2015

"ሰው ብቻ አትሁኑ"

"ሰው ብቻ አትሁኑ"
መጋቤ ሐዲስ እሸቱ

"ሰው ብቻ አትሁኑ...ሰው ብቻ ማለት ምንድን ማለት ነው? ብዬ ሳስብ፤ የሚበላ፣ የሚጠጣ፣ በሚለብሰው ልብስ፣ በሚነዳው መኪና የኑሮን ስኬት የሚለካ ማለት ነው።
እስከ ሞት የሚኖር ማለት ነው፦ እንደ እንስሳ።

"...ታላቁ ሊቅ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዲህ ይላል 'ሰው እግዚአብሔር ሲለየው' ይላል። ሰው እግዚአብሔር ሲለየው፤ ጠባዩ እንደ አራዊት፤ አመጋገቡ እንደ እንስሳ፣ ሆኖ መልኩ ብቻ የእግዚአብሔር ሆኖ ይቀራል። በጣም ቀለል ባለ አገላለጽ ሲም ካርዱ የወጣ ሞባይል(mobile ) ማለት ነው ። ጥሪ የማይቀበል፤ ለጉትቻ ማንጠልጠያ ብቻ የተሰራም ጆሮ አለ።"


"...እኔ በዕውነቱ ከተማው ፈርሶ እየተሰራ ነው እየተባለ ዐይናማዎቹ ሲያወሩም ሲያስወሩም እሰማለው። ፈርሶ መሰራት ያለበት የሰዉ አስተሳሰብ ነው።... የሰዉ አስተሳሰብ ፈርሶ ካልተሰራ፤ የተሰራ ከተማ ይፈርሳል። ጃፓንና ቻይና ሀገራቸውን ያለሙት መጀመሪያ አስተሳሰባቸውን አልምተው ነው። አስተሳሰቡ ያልለማ ሕዝብ የለማውን ያወድማል።"
"ቤታችሁ ገብታችሁ እንድታጤኑት ነው። እነዛ... (ምንትስ) የምንላቸው ክርስቲያኖችን አርደዋል... ምዕራባውያኑ ደግሞ ክርስትናን እራሱን አርደውታል።....ወንድ ለወንድ፣ ሴት ለሴት፣ በቤተክርስቲያናቸው እያጋቡ፤ ክርስትናን አጋድመው ያረዱ ምዕራባውያን ናቸው። (ይህን ሁሉ ያመጣውም) የምዕራባውያን ልክ ያጣ ነጻነትና ገደብ ያለፈ ዝርክርክነት ነው።"
"እንደምታዩት እኔ ዐይነ ስውር ነኝ። ቀላል አይደለም.... እንክዋን ዘውትር ዓይን አጥቶ አንድ ቀን መብራት ሲሄድ ስንት እንደምታማርሩ ታውቅታላችሁ። አንድ ቀን ግን አልቅሼ አላውቅም። ከሞት ወዲያ መብራት አለ። ከመቃብር በላይ መብራት አለ። ... ወደ መቃብር ሲወርድ ማንም ዓይነ ስውር ነው። ማንም ዐይኑ እያየ የተቀበረ የለም። ተስፋችን ግን ምንድን ነው? ከሞት ወዲያ ሕይወት አለ። ከሞት ወዲያ ብርሃን አለ።"
"...አንድ አንድ ጊዜ እመኛለሁ። የማይረባ ነገር ስናይ (ዓይናችንን) የሚያጠፋ ቆጣሪ ቢኖር... መልካም ነገር እስክናይ ድረስ ለጊዜው የሚያጠፋ ቆጣሪ ቢኖር።
"አሁን እንደው ጆሮ በካርድ የሚሰራ ቢሆን ሐሜት እንሰማ ነበር?(ከፍተኛ ሳቅ)...
የምንፈልገውን (ብቻ) አውርተን ስዊች ኦፍ እናደርገው ነበር። ስንት ዞማ ጸጉር ይዞ አስተሳሰቡ የከረደደ አለ።
"ጀርመን ሀገር ሄጄ ሲነግሩኝ፤ ባለ አምስት ኮከብ የውሻ ሆቴል አለ ተባለ። እኛ ሀገር አምስት ኮከብ ሆቴል ገብተው የበሉ ትንሽ ዝና (ሀብት) እና ትንሽ ሥልጣን ያላቸው ናቸው። ማን ይገባል ከነሱ ውጪ። ግን ሰዋች ነን። የጀርመን ውሻ
ዛሬም ውሻ ነው ለዘላለምም ውሻ ነው። እኛ ግን ሰው ነን። እንደ ሰው አስቡ (ምዕመናን) በማርያም።"
"...የንጉሠ ነገሥቱ የክርስቶስ አልጋ ወራሾች ነን... የደስታችሁ ልኬት የደስታችሁ ሚዛን ምግብና መጠጥ አይሁን፤ መኪናና ቤት ዝናንም አታርጉ። እኛ መለኪያችን
ጽድቅ ነው። መከኪያችን መንግሥተ ሰማያት ነው። ያ የምንገባበት ቤት ደግም የተዋበ፣ የደመቀ፣ መብራት ውሀ የማይሄድበት፤ 24 ሰዓት ክርስቶስ የሚያበራበት፤ 24 ሰዓት የሕይወት ውሀ የሚጠጣበት፤ ሀብታም፤ ደሀ፣ ተራሰው የማይባልበት፣ እገሌ ግባ እገሌ ውጣ የማይባልበት ቦታ ነው።

Sunday, 28 June 2015

I need my dad to be here, pleads daughter Helawit Andargachew

I need my dad to be here, pleads daughter

Philip Hammond warns Ethiopia over treatment of Briton on death row

Foreign secretary condemns detention of Andargachew Tsige in solitary confinement with no access to consular help or right to appeal

The treatment of a Briton on death row in Ethiopia is threatening to undermine the country’s relationship with the UK, the foreign secretary has warned.
In an unusually blunt statement, Philip Hammond has called for rapid progress in the case of Andargachew Tsige, who is being held in solitary confinement in an unknown location in Ethiopia.
The foreign secretary’s comments, released a year after Tsige was abducted while transiting through Yemen, is a clear sign of official disapproval of the approach taken by the regime in Addis Abbaba. The Foreign Office is escalating the case beyond confidential diplomatic exchanges.
On Wednesday, Hammond spoke to the Ethiopian foreign minister, Tedros Adhanom Ghebreyesus, about the case on the phone. His statement said: “I am deeply concerned that, a year after he was first detained, British national Andargachew Tsige remains in solitary confinement in Ethiopia without a legal process to challenge his detention.
“I am also concerned for his welfare and disappointed that our repeated requests for regular consular access have not been granted, despite promises made.
“I spoke to foreign minister Tedros and made clear that Ethiopia’s failure to grant our repeated and basic requests is not acceptable. I informed Dr Tedros that the lack of progress risks undermining the UK’s much valued bilateral relationship with Ethiopia.
“I asked Dr Tedros once again to permit immediate regular consular access and for our concerns regarding Mr Tsige’s welfare to be addressed. I have also asked that the Ethiopian authorities facilitate a visit by Mr Tsige’s family. Foreign Office officials will continue to provide consular support both to Mr Tsige and to his family during this difficult time.”
Tsige’s partner, Yemi Hailemariam, also a British national, lives in London with their three children. She has spoken to him only once by phone since his abduction.
“He’s in prison but we have no idea where he is being held,” she told the Guardian last month. “He said he was okay, but I’m sure the call was being listened to. He had been in Dubai and was flying on to Eritrea when the plane stopped over in Yemen. He hadn’t even been through immigration. We think Yemeni security took him and handed him over to the Ethiopians.
“They say there was an extradition agreement, but it was so quick there was no time for any semblance of a legal hearing. Yemen and Ethiopia had close relations then. The [Ethiopian] government have put him on television three times in heavily edited interviews, saying he was revealing secrets.
“He has been kept under artificial light 24 hours a day and no one [other than the UK ambassador] has had access to him.”
Tsige, 60 – known as Andy – had previously been secretary general of Ginbot 7, a political opposition party that called for democracy, free elections and civil rights. He first came to the UK in 1979.“He has been kept under artificial light 24 hours a day and no one [other than the UK ambassador] has had access to him.”

The Ethiopian government has accused him of being a terrorist. In 2009, he was tried with others in his absence and sentenced to death. The latest reports suggest that his health is deteriorating. 
His lawyer, Ben Cooper, of Doughty Street Chambers, said: “We welcome the Foreign Secretary condemning the illegality of Andy Tsige’s detention, confirming the fact of his solitary confinement and demanding consular visits. But we have a simple ask: please request Andy Tsige’s return home to his family in London. Mr Tsige was kidnapped by Ethiopia at an international airport and the only remedy for kidnap is release. Why has Mr Hammond not yet asked Ethiopia to release Andy so he can return home to England?”
Juan Méndez, the UN special rapporteur on torture, has written to the Ethiopian and UK governments saying he is investigating Tsige’s treatment. 

Who is Andargachew Tsige?


Andargachew, or Andy, Tsige fled Addis Abbaba in the 1970s following threats against his life from the military regime, the Derg, which then controlled Ethiopia.
A student activist, he had attracted the attention of the authorities. His younger brother was killed by the security forces. Tsige escaped into the mountains to join opposition groups.
In 1979, after falling out with fellow rebels, he sought asylum in the UK. He studied at the University of Greenwich and obtained full UK citizenship. 
Tsige returned to Ethiopia after the Derg was overthrown but moved back to the UK in the early 1990s where he became active in opposition politics. 
In 2005, he returned to Addis Abbaba again. He took part in that year’s election and was briefly imprisoned. after being freed, he founded a new political movement, Ginbot 7, from his exile in London.
The organisation was alleged by the Ethiopian government to have launched a failed coup in 2009. Tsige was condemned to death in his absence.
In June 2014, he had flown to the Gulf to give lectures. An unexpected change to his return route saw him fly back via Yemen where he changed planes. At Sana’a airport, he was arrested by guards and put on a plane to Ethiopia on the grounds that there was an extradition agreement between the two countries.
Supporters say that had he been born white and in the UK, the Foreign Office would have taken a more forceful line in campaigning for his release from death row in east Africa.
His partner, Yemisrach Hailemariam, and their three children live in London. She has campaigned actively for his freedom. 
In February a delegation of MPs, led by Jeremy Corbyn, his local member, was scheduled to visit Ethiopia in an attempt to secure his release. The trip was abandoned following a meeting with the Ethiopian ambassador.

Tuesday, 19 May 2015

ጉዳዩ፡ፕሮግራም ስለማቋረጥ





ርጅታችን ከጣቢያችሁ የአንድ ሰዓት የስርጭት ጊዜ በመውሰድ በ ኢቢኤስ ቴሌቪዥን ላለፉት ሁለት ዓመታት “ጆሲ ኢን ዘ ሃውስ ሾው ” የተሰኘ ፕሮግራም እያቀረበ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ ፕሮግራሞቻችን ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው፤ ትውልድን የሚያንጹና የሚያስተምሩ በመሆናቸው በአጭር ጊዜ ውስጥ በተመልካች ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነት ለማግኘት የቻሉ እንደሆነ አያጠራጥርም፡፡ቀደም ባለው ጊዜ በተፈቀደልን የአየር ሰዓት የሠራናቸውን ፕሮግራሞች ለማቅረብ የነበሩት ሁኔታዎች የተመቻቹ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ግን አየር ላይ እንዲውሉ ከላክናቸው ፕሮግራሞች አንዳንዶቹ በተፈቀደልን የአየር ሰዓትና ጊዜ እንዳይተላለፉ ተደርገዋል፡፡

ጆሲ መልቲሚዲያ የሚያዘጋጃቸው ፕሮግራሞች የአየር ሰዓት ለመሸፈን ብቻ ተብለው የሚዘጋጁ ሳይሆን እያዝናኑ የሚያስተምሩ ኢትዮጽያዊ አንድነትን የሚያጠነክሩ ፤የትላንትን ታሪክ የሚያውሱና ትውልድ የሚቀርጹ፤ መረዳዳትንና መተጋገዝን የሚሰብኩ ናቸው ፡፡ 

በአብዘኛው የአፍሪካ ሀገራት በቅኝ አገዛዝ መዳፍ ውስጥ በነበሩት ወቅት ሀገራችን ኢትዮጵያ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም የጣልያንን ወራሪ ጦር ያሸነፈችበት የአድዋ ድል 119ኛ ዓመትን ምክንያት በማድረግ በድሉ እንደሚኮራ እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ በያገባኛል ስሜት ደክመን የሠራነው የአድዋ ድል መታሰቢያ ፕሮግራም በተፈቀደልን ቀንና የአየር ሰዓት እሁድ የካቲት 29 ቀን 2007 ዓ.ም ከሁለት ሰዓት እስከ ሶስት ሰአት እንዳይተላለፍ ተደረጎብናል ፡፡ይህ ያልተለመደ ነገር ሲከሰት ብናዝንም ቀደም ሲል የነበረንን መልካም የሥራ ግኑኙነት ከግምት ውስጥ በማስገባትና ወደፊትም እንደማይደገም በማመን ነገሩን በትዕግስት አልፈን አብረን ለመስራት ሞክረን ነበር፡፡

ይህ መፈጠሩ እያሳዘነን እያለ ሌላ ነገር ተከሰተ፡፡ ድርጅታችን በጣቢያቸሁ ፕሮግራም ማስተላለፍ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ በተለይ በሀይማኖታዊና በዘመን መለወጫ በዓላት ላይ በተለያየ ጊዜና ሙያ ሀገራቸውን ያገለገሉ ግን ደግሞ የተዘነጉ የሀገር ባለውለታዎችን መጠየቅና የተቻለውን ያህል ድጋፍ ማድረግ የተለመደ ነበር፡፡በእዚህም መሰረት የ2007 ዓ.ም የትንሣኤን በዓልን ምክንያት በማድረግ ያዘጋጀነው ፕሮግራም በቂና አሳማኝ ባልሆነ ምክንያት እንዳይተላለፍ ተደርጎብናል፡፡

ፕሮግራማችን በተደጋጋሚ በተለመደው የአየር ሰዓት እንዳይተላለፍ መደረጉ እያሳዘነን እያለ ፤በየመን ፤በደቡብ አፍሪካ በተለይም በሊቢያ አይ.ኤስ የተባለው ፅንፈኛ ቡድን በንጹሃን ዜጎቻችን ላይ ያደረሰውን ጥቃት ተከትሎ እንደ ኢትዮጵያዊ አዝነን ፤ቤተሰቦቻቸውን እና ዘመዶቻቸውን በሞት ከተነጠቁ ሀዘንተኞች ጎን ሆነን ሀዘናችን ገልጸንና የሀዘናቸው ተካፋይ ሆነን ድጋፍም አድርገን በተጨማሪም በኢትዮጵያዊ አንድነት ፤በሀይማኖት እኩልነት ፤ተፈቃቅሮ ፤ተቻችሎና ተከባብሮ በመኖር፤ እርስ በእርስ በመረዳዳት እንዲሁም ዜጎቻችንን ለእንግልትና ለሕልፈተ ሕይወት እየዳረገ ባለው ሕገ ወጥ ስደትና ሕገ ወጥ ደላሎች ዙሪያ ደክመን የሰራነው አስተማሪ ፕሮግራም ከጣቢያው በወሰድነው የአየር ሰዓት ላይ በተደጋጋሚ እንዳይተላለፍ መደረጉ ወደፊት አብሮ የመስራታችንን ነገር በጥርጣሬ እንድንመለከተው አድርጎናል ፡፡ 

ፕሮግራማችን በጣቢያችሁ ላይ መቅረብ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ለነበረን መልካም ግንኙነት ከልብ እናመሰግናለን፡፡ ከላይ ከጠቀስናቸው ችግሮች በተጨማሪ ሌሎችም ምክንያቶች ቢኖሩም የስራ ግኑኝነታችን እንዲቀጥል ስምምነት ለማድረግ ብንሞክርም አልተሳካም ፡፡ በእናንተ በኩል እየተከናወነ ያለው ያልተለመደ ተግባር የስራ ግኑኝነታችን እንዲቋረጥ ከፍተኛ ፍላጎት ያለ እንደሆነ እንድናምን ስላደረገን በእኛም በኩል ይህንን በአጽንኦት እንድንመለከተው አስገድዶናል፡፡

ከእዚህ በተጨማሪ ውል ተፈራርመን መስራት ሲገባን በድርጅታቸሁ አሰራር መሰረት ያለፈውን አንድ ዓመት ያለ ውል መስራታችን ይታወቃል ፡፡ ከአሁን በኋላ ግን በእዚህ አሰራር መቀጠል አንችልም ፡፡ ስለሆነም ከስፖንሰሮቻችን ጋር እስከ ሲዝን 4 የመጨረሻ 13ኛ ክፍል ድረስ የተደረገውን ውል ከግምት ውስጥ በማስገባት እስከ ግንቦት 30 ቀን 2007 ዓ.ም ድረስ ፕሮግራማችን በጣቢያቸሁ እንዲተላለፍ በእኛ በኩል አስቀድመን ዝግጅታችንን የጨረስን መሆናችንን እያሳወቅን፤ ከግንቦት 30 ቀን 2007 ዓ.ም ጀምሮ በጣቢያቸሁ ሲተላለፍ የነበረው “ጆሲ ኢን ዘ ሃውስ ሾው” የተሰኘው ፕሮግራማችን በእናተው አስገዳጅነትና ተገቢ ያልሆነ አሰራር እንደምናቋርጥ አስቀድመን እናሳውቃለን ፡፡

ከሰላምታጋር

Sunday, 26 April 2015

ጌትነት እንየው የኪነጥበብ ባለሙያዎች የሀዘን መግለጫ ስነ ስርዓት ላይ “እኛው ነን “ በሚል ርዕስ ያቀረበውን ግጥም ይመልከቱ



እኛው ነን
(በጌትነት እንየው)


እኛ ነን; እኛው ነን; እኛ የዛሬዎች
በአጭር የተቀጩ ሩቅ መንገደኞች
ሰላሳ ህልመኞች፣ ሰላሳ ተስፈኞች፣ ሰላሳ ወጣቶች
ሀገር እንደሌለው በሰው ሀገር ምድር ሲቀላ አንገታቸው
ወገን እንደ ሌለው ከሰው ሀገር ባህር ሲቀየጥ ደማቸው
በአገር ቁጭ ብለን ከአለም ጋራ እያየን
ከሬት የመረረ ከቋጥኝ የሚከብድ
ከቶን የሚያቃጥል ከብራቅ የሚያርድ
ሀገር ያህል መርዶ በሰንበት አመሻሽ በአገር የተሸከምን
በገዛ ሞታችን እዝን የተቀመጥን፡፡
ካሳለፍነው ህይወት ካለፈው መከራ
መማር የተሳነን ደመና ወራሾች፣
የሞትነውም እኛ ያለነውም እኛ
ከፋይም ተቀባይ እኛው ነን ባለእዶች፡፡


እኛው ነን….


ከቅጣትም ቅጣት ከመርገምትም መርገት፣
የገዛ አንገታችን በስለት ሲቀላ
የገዛ ደማችን ባህሩን ሲያቀላ
የራሳችንን ሞት ቆሞ መመልከቱ፣
ምን ያህል ነው ፍሙ ምን ያህል ይከብዳል ሰቆቃው እሳቱ?
ምን ያህል ነው ሸክሙ? ምን ያህል ይዘፍቃል? መከራው ክብደቱ
ምን ያህል ይጠልቃል? ምን ያህል ይሰማል? መጠቃት ስለቱ
ሀዘን ነው? ቁጣ ነው? ጸጸት ነው? ምንድነው መጠሪያው?
ምንድነው ስሜቱ?
እውን ይህን መአት ይኼን የእኛን መቅሰፍት
ቋንቋዎች በቃላት ችለው ይገልጹታል?
እውን ይህ ስቃይ፣ ይህንን ሰቆቃ፣ እናትና ሀገር ሸክሙን ይችሉታል?


እኛው ነን እኛው ነን…


ለዚህ ክፉ እጣችን ለዚህ መርገምታችን
ለአለም ለፈጣሪ አልፈታ ላለው እንቆቅልሻችን
መነሻም መድረሻም ጥያቄዎች እኛ መልሶችም እኛው ነን፡፡
እኛው ነን የገፋን፣ እኛው ነን የከፋን
እኛው ነን ያጠፋን ፣እኛው ነን ያጠፋን፡፡
ከዘመን ጋር አብሮ መዘመን ተስኖን
ሰፊ አገር ይዘን በሀሳብ እየጠበብን
በፍቅር ተሳስቦ አብሮ መራመዱ አቀበት የሆነን
ቂም እየቆነጠርን፣ ቂም እየመነዘርን
በዛሬ መንጋጋ የትናንቱን ድርቆሽ የምናመነዥክ
በዛሬ ምድጃ የትናንቱን አመድ ታቅፈን የምንሞቅ
ባንድ ላይ ከመጓዝ በየፊና ሩጫ አረፋ ምንደፍቅ


እኛው ነን እኛው ነን….


ከእምነት የተፋታን ከፈጣሪ የራቅን፡፡
እኛው ተጋፊዎች፣ እኛው ተገፊዎች
እኛው አሳዳጆች፣ እኛው ተሳዳጆች
ካሳለፍነው ህይወት ካለፍነው መከራ
መማር የተሳነን ደመና ወራሾች
እኛው ነን እኛው ነን እኛ የዛሬዎች
የነገ፣ የታሪክ ያገር ባለእዳዎች፡፡


እኛው ነን….


በንፍገት በስስት በስግብግብ መዳፍ
ከድሆች ጉሮሮ ካፋቸው መንጭቀን
ሌሎችን ረግጠን ሌሎችን ጨፍልቀን
በሌሎች ጀርባ በሌሎች ጫንቃ ላይ ወደ ላይ መሳቡ ቅንጣት የማይጨንቀን
በማስመሰል ጥበብ በአድርባይ አንደበት በሸፍጥ የሰለጠን
ከብዙዎች ድርሻ ተሻምተን ተናጥቀን
ላንድ ለራሳችን በወርቅ ላይ አልማዝ በህንጻ ላይ ህንጻ
ስንቆልል ስንከምር የማይሰቀጥጠን፣
የመንፈስ ድውዮች የንዋይ ምርከኞች
የወንበር ሱሰኞች የሆድ አምላኪዎች
ከሰውነት ወርደን በነፍስ የኮሰመን የስጋ ብኩኖች
የራሳችን ሀጢያት የራሳችን ሲኦል እኛው ነን መርገምቶች


እኛው ነን!


በዚህ ሁሉ ግና …..
መቼም ቢሆን መቼ ሰው ይሞታል እንጂ ተስፋ አይሞትምና
በመንገድ የቀሩት ወጣቶቻችን
በአጭር የተቀጨው ሀሳብ ምኞታቸው
ተስፋ አለን ተስፋቸው፡፡
በአገራቸው አፈር በታናሾቻቸው
ነገ ውብ ይሆናል ለምልሞ ይጸድቃል በዛሬው ደማቸው
ዛሬ የመከነው ውጥን ርዕያቸው
በጊዜና በአገር ነገ እውን ይሆናል ይፈታል ህልማቸው
ይህ ነው መጽናኛችን ይህ ነው መዕናኛቸው፡፡