Thursday 29 January 2015

ኢትዮጵያ የወሲብ ቱሪዝም ማግኔት እየሆነች ነው


‹‹Ethiopia has become a magnet for sex tourism›› (ኢትዮጵያ የወሲብ ቱሪዝም ማግኔት እየሆነች ነው) በማለት ይገልጻታል፡፡ አንድ ዓለም አቀፍ ሪፖርት

መነሻ በቅርቡ ማክቤዝ ሚዲያ ኮሚኒኬሽን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና ኤች አይ ቪ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ወሲባዊ ንግድ የሚፈጸምባቸው ማሳጅ(መታሻ) ቤቶች መስፋፋት በወጣቶችና በሴቶች ላይ የሚያስከትሏቸው አሉታዊ ተፅዕኖዎች በሚል ርዕስ አንድ ጥናት አሰርቶ ነበር፡፡ ወሲብና ወሲባዊ ተግባራት የሚፈፀምባቸውን ማሳጅ ቤቶች በተመለከተ bማህበራዊ ስነልቦና ባለሙያዎቹ አቶ በላይነህ ዘለለውና አቶ ዮሴፍ አህመድ የተደረገው ጥናት እንደሚያሳየው በአዲስ አበባ ከተማ በተለይም ቦሌ ክፍለ ከተማ ውስጥ የሚገኙ መታሻ (ማሳጅ) ቤቶች ውስጥ ህገ ወጥ የሆኑ ማሳጅ ቤቶች በአሳሳቢ ደረጃ ተስፋፍተዋል፡፡ ማሳጅ ቤቶች ለወሲብ ቱሪዝም መስፋፋት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ 

እንደሚታወቀው አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የተለያዩ ሃገራት ዲፕሎማቶችና የውጭ ሃገር ድርጅት ሰራተኞች በብዛት ይኖራሉ፡፡ ትላልቅ አህጉር አቀፍና ዓለም አቀፍ ስብሰባዎችና ጉባኤዎች በተደጋጋሚ ይደረጋሉ፡፡ በነዚህ ጉባኤዎች ላይ ለመሳተፍ የሚመጡ የባህር ማዶ ሰዎች በአብዛኛው ጊዜ አዳራቸውን የሚያደርጉት በህገወጥ ማሳጅ ቤቶችና በትላልቅ ሆቴሎች ውሰጥ በግዥ ከሚቀርቡላቸው ሴተኛ አዳሪዎች ጋር አንዳንዴም በደላሎች አማካኝነት ከሚቀርቡላቸው የቤት ልጆች ጋር እንደሆነ ይነገራል፡፡ በዚህ ሂደት በገንዘብ ተጠቃሚ የሚሆኑ በርካታ ሰዎች አሉ፡ ፡ በወጣት ሴቶች ስነልቦና እና ስነተዋልዶ ጤና እንዲሁም በማህበረሰቡ ግብረገባዊ አስተሳሰብ ላይ የሚነግዱ፣ ኢ - ሞራላዊና ህገ ወጥ በሆነ መንገድ ገንዘብ የሚሰበስቡ ማሳጅ ቤቶች ድርጊት በጣም አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል ይላል ጥናቱ፡፡ ይሁንና ችግሩን ለመፍታት የተደረጉ እንቅስቃሴዎች የሉም ወይም አነስተኛ ናቸው፡ ፡ የዚህ ጽሁፍ አላማ ጥናቱን ጨምቆ በማቅረብ የጉዳዩን አሳሳቢነት በማሳየት የሚመለከታቸው አካላት በፍጥነት ወደተግባራዊ እርምጃ እንዲገቡ ግፊት ማድረግም ነው፡፡ 

16ኛው “ዓለም አቀፍ የኤች.አይ.ቪ/ኤድስ እና የአባላዘር በሽታዎች ጉባኤ በአፍሪካ” (16th International Conference on AIDS and STLs in Africa – ICASA) ከሦስት ዓመት በፊት በኢትዮጵያ እንደተስተናገደ ይታወሳል፡፡ከዚያ ቀደም ብሎ ብዙ ኢትዮጵያውያንን ያስደነገጠና ያወዛገበ አንድ ስብሰባ ሊደረግ ታስቦ ነበር፡፡ “የአፍሪካ ግብረ ሰዶማውያን የቅድመ ኮንፈረንስ ማነቃቂያ ስብሰባ” የተባለው ይህ ስብሰባ በተለይ በሃይማኖት ተቋማት ከፍተኛ ውግዘት ገጥሞት ነበር፡፡ በማህበራዊ ድረ ገጾችና በተለያዩ የሃገር ውስጥ ጋዜጦችና መጽሔቶች (ቁም ነገር መጽሔትን ጨምሮ) ብዙ ፅሁፎች በጉዳዩ ዙሪያ ወጥተው ነበር፡ ፡ ለግብረ ሰዶማውያን መስፋፋትና የወሲብ ቱሪዝም እየጨመረ እንዲመጣ ከሚያደርጉ አባባሽ ነገሮች አንዱ የህገ ወጥ ማሳጅ ቤቶች መኖር ነው፡፡ እንደ ታይላንድ ያሉ ሃገራት ለዚህ ምሳሌ መሆን ይችላሉ፡፡ የወሲብ ቱሪዝም ‹ማግኔት› 

በቅርቡ በወጣ አንድ ዓለም አቀፍ ሪፖርት ላይ ኢትዮጵያ የወሲብ ቱሪዝም እየተስፋፋባቸው ከመጡ ሃገራት አንዷ መሆኗን ‹‹Ethiopia has become a magnet for sex tourism›› (ኢትዮጵያ የወሲብ ቱሪዝም ማግኔት እየሆነች ነው) በማለት ይገልጻታል፡፡ ዓለም አቀፍና አህጉር አቀፍ ጉባኤዎችንና ስብሰባዎችን ማስተናገዷ እያስገኘላት ከሚገኘው ኢኮኖሚያዊ ገቢ በተጻራሪ ለማህበራዊ ችግሮች እየዳረጋት መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ ወደ ሃገሪቱ የሚገቡ የውጭ ሃገር ጎብኝዎችና የጉባኤ ተሳታፊዎች ለመጤ ባህሎች እያጋለጧት ነው፡፡ በመጠጥ ቤቶችና በተለያዩ የአዲስ አበባ ጎዳናዎች የሚዘወተረው ወሲባዊ ንግድ ወደ መኖሪያ ቤቶችም ገብቷል፡፡ በተለይ የእንግዳ ማረፊያ ተብለው የተዘጋጁ አንዳንድ ቤቶች ለህገ ወጥ ማሳጅ ቤቶችና ለወሲብ ንግድ መፈጸሚያነት እየዋሉ  ነው፡፡

እንደ ተባበሩት መንግስታት የዓለም የቱሪዝም ድርጅት (UNWTO) ‹‹ የቱሪዝምን ቅርጽ እና መረብ በመጠቀም በማንኛውም የወሲብ ነክ እንቅስቃሴ ላይ ለመሳተፍ የሚደረግ ጉዞ ›› የወሲብ ቱሪዝም ወይም ዘመናዊ የወሲብ ንግድ ነው ሲል ይገልጻል፡፡ 

በዓለማችን ከቅርብ አሥርት ዓመታት ወዲህ የወሲብ ቱሪዝምን ህጋዊ ማዕቀፍ እንዲኖረው በማድረግ ለሃገሪቱ እንዲሁም ለዘርፉ ተዋንያን ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ሊያመጣ በሚችል መልኩ እየተጠቀሙበት ይገኛሉ፡፡ 

ከእነዚህ ሃገራት ውስጥ ጀርመን፣ ብራዚል ፣ሞሮኮ፣ ዶሚኒካን ሪፐብሊክ እንዲሁም በምርጥ የእግር ኳሰኞቿ የምናውቃት ኔዘርላንድስ ከአጠቃላይ የሃገራቸው ኢኮኖሚ ከ ሁለት እስከ አምስት በመቶ የሚሆነውን ከዚሁ ዘርፍ ይሸፍኑበታል፡፡ 

ይህ ዘርፍ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ በርከት ያሉ አገልግሎት ሰጪዎችን የሚያቅፍ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ አየር መንገዶች፣ሆቴሎች የየብስ ትራንስፖርት ተቋማት የመሳሰሉት ተጠቃሽ ናቸው፡ ፡ 

ከዚህ በተጨማሪ እነዚሁ ሃገራት በድርጊቱ ለሚሳተፉት ሴት ዜጎቻቸው የማህበራዊ ዋስትናን እስከ ጡረታ ድረስ በመስጠታቸው ድርጊቱ የሚያስከትለው ማህበራዊ ቀውስ ዝቅተኛ ቢሆንም ሞራላዊ ተጠያቂነቱ ግን ከፍ ያለ ነው፡፡ 

በሃገራችን በተለይም በመዲናችን እና በተለያዩ የቱሪስት መናኸሪያ በሆኑ አካባቢዎች ከራቁት ጭፈራ ቤቶች የጀመረው ይህ የዘመናዊ የወሲብ ንግድ (የወሲብ ቱሪዝም) በአሁኑ ሠዓት በርከት ያሉ የወሲብ ንግድ ተቋማትን፣ ሰፊ የድርጊቱ መረብ፣ እሳት የላሱ ደላሎችን እንዲሁም ሰፋ ያለ ካፒታል የሚያንቀሳቅስ እና ወደ ኢንዱስትሪ ደረጃ ሊሸጋገር የደረሰ ተግባር ሆኗል፡፡ 

በተለይም የሃገራችን የዲፕሎማሲ እንቅስቃሴ እየተጠናከረ በመጣበት በአሁኑ ወቅት እየጨመረ ያለውን የወጭ ሃገራት ዜጎችን ፍሰት ተከትሎ ዘርፉ ጠንከር ወደማለት እና የአደባባይ ሚስጥር በሚባለው ደረጃ ላይ ለመድረስ ችሏል፡፡ 

እነዚህ የወሲብ ንግድ ማዕከላት በዘርፉ ተዋንያን እና ቅርበት ባላቸው ወገኖች ዘንድ ‹‹ፍርድ ቤት ›› በመባል የሚታወቁ ሲሆን የድርጊቱ ተሳታፊ ሴቶች ደግሞ ከፈረንሳይኛ ቃል በተወረሰ ነገር ግን ከድርጊቱ ጋር ምንም ተዛምዶ በሌለው ‹‹ትራባዪ›› በሚል ስያሜ ይታወቃሉ፡፡ 

እነዚህን ‹‹ፍርድ ቤቶች›› እና ‹‹ትራባዪዎች›› ከውጭ ሃገራት ዜጎች ጋር በማገናኘት ረገድ የአንበሳውን ሚና የሚጫወቱት ደላሎች በተለምዶ ‹‹ጋይድ››የሚባሉ ሲሆን የትራባዪዎች (የወሲብ ንግድ ተሳታፊ ሴቶች) ማደሪያ እና መዋያ ቦታ የወሲብ ንግድ ማዕከላቱ ‹‹ፍርድ ቤቶቹ›› ናቸው፡፡ 

አንድ ፍርድ ቤት በውስጡ ከ 15-20 ለሚሆኑ ‹‹ትራባዪዎች›› ደንበኞቻቸው እስኪመጡ የሚገለገሉበት የማደሪያ አልጋ እና ሌሎች ቁሳቁሶችን የሚያሟሉ ሲሆን ለሚጎበኟቸው የውጭ ሃገራት ዜጎችም በውድ ዋጋ የሚሸጡ መጠጦችን ለሽያጭ ያቀርባል፡፡ አንድ የውጭ ሃገር የወሲብ ደምበኛ የመረጣትን ‹‹ትራባዪ›› ከፍርድ ቤቱ ለአንድ አዳር ወይም ውሎ ይዞ ለመውጣት ከአንድ ሺህ እስከ አምስት ሺህ ብር የሚከፍል ሲሆን እንደየ ፍርድቤቱ ህግ ደግሞ ተጨማሪ የመውጫ የኮቴ የመሳሰሉትን ክፍያ መክፈል ይጠበቅበታል ፡፡ 

ለአንድ አዳር ወይም ውሎ የተስማማች አንድ ‹‹ትራባዪ›› ሊከፈላት ከተስማማችው የብር መጠን ውስጥ ከ50-70 በመቶ የሚሆነው በወሲብ ተቋሙ ባለቤት እና በደላሎች የሚወሰድ ነው፡፡ 

እነዚህ የወሲብ ንግድ ተቋማት በአብዛኛው በትላልቅ ቪላ ቤቶች የሚገኙ ሲሆን በተለይም ከቦሌ ድልድይ እስከ ደምበል፣ በሃያ ሁለት ፣ሲኤምሲ፣ መስቀል ፍላወር እንዲሁም የቱሪስት እንቅስቃሴ በሚበዛባቸው አካባቢዎች ተበራክተው ይገኛሉ፡፡ 

ይህ የወሲብ ቱሪዝም ወይም የወሲብ ንግድ ከወሲብ ንግድ ተቋማቱ ባለፈ መሸታ ቤቶችን፣የጫት ማስቃሚያ ቤቶችን ፣ የእንግዳ ማረፊያዎችን እንዲሁም ሌሎች መሰል ተቋማትን በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ እንደማስተሳሰሩ መጠን የሚያዘዋውረው የገንዘብ መጠን ከፍተኛ ቢሆንም ከዚህ ዘርፍ መንግሥትም ሆነ የድርጊቱ ተሳታፊ ሴት እህቶቻችን የሚያገኙት ጥቅም ዘላቂነት ያለው እና ቀጥተኛ ባለመሆኑ በህብረተሰቡ ላይ የሚፈጥረው ማህበራዊ ቀውስ ከፍተኛ ነው፡፡ 

ምንም እኳን ይህ ተግባር በኢትዮጵያ ህጎች የተከለከለ ቢሆንም ድርጊቱን ከመቆጣጠር አኳያ የመንግሥት ጥረት ዝቅተኛ የሚባል ነው፡፡ ለዚህም በከተማችን በርክተው የሚገኙት እነዚህ የወሲብ ንግድ ተቋማት ምስክሮች ናቸው፡፡ 

በዚሁ በወሲብ ንግድ ላይ በሁለት ጎራ የተከፈሉ አስተያየት ሰጪዎች የሚደመጡ ሲሆን በአንደኛው ወገን ድርጊቱ የሃገሪቱን መልካም ስም እና የማህበረሰቡን ሞራል የሚነካ በመሆኑ የቱንም ያህል ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ቢያመጣ ሊወገዝ እና ቁጥጥር ሊደረግበት የሚገባ ተግባር ነው ሲሉ የሚሞግቱ አሉ፡፡ በሌላኛው ጎራ ይህን ተግባር ማስቆም ለሚጠይቀው ቁርጠኝነት ከፍተኛ ትኩረት መስጠት አሊያም ድርጊቱ ይፋዊ በሆነ መንገድ ተፈቅዶ ከድርጊቱ ተዋንያን ከግብር እና ከሌሎች የአገልግሎት ክፍያዎችን በመሰብሰብ የሚገኘውን ገቢ በመጠቀም ድርጊቱ የሚፈጥረውን ማህበራዊ ቀውስ መቀነስ ተገቢ ነው ባዮች ናቸው፡፡ 

የማሳጅ ታሪካዊ ዳራ የማሳጅ ታሪካዊ አመጣጥ በብዙ ሀገሮች የብዙ ሺህ ታሪክ ያስቆጠረ ነው፡፡ በጥንታዊ ጽሑፎች ላይ ተጽፎ እንደሚታየው በምስራቃዊያንና በምዕራባዊያን ስልጣኔ ሰዎችን ለመፈወስና ለማሻል ሰዎችን በመንካት/በማሸት/ እንደሚያደርጉ ታሪካዊ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ አብዛኛውን በአሁኑ ሠዓት የምንጠቀመው የማሳጅ ዘዴዎችና አቀራረቦች አጀማመራቸው ከጥንቱ የማሳጅ ዘዴዎች ነው፡፡በጥንት ጊዜም ቢሆን ማሳጅን የሰዎችን ህመም ለማሻል፣አደጋን ለማሻል(ጉዳቱን ለመቀነስ)፣ሰዎችን ሰውነታችውንና አዕምሮአቸውን ዘና ለማድረግ(ለማዝናናት) እንዲሁም ህመምን ለመከላከልና ለማዳን ሲጠቀሙበት ነበረ፡፡

 በምስራቁ ዓለም የማሳጅ ታሪክ እንደሚያሳየው ማሳጅ እንደ መለኮታዊ ተዓምር/ Divinely- created system/ ተደርጎ የሚታይበት ሁኔታ ነበር፡፡በህንድ ሀገር ማሳጅን አይሩቨዳ / Ayurveda/ ብለው ይጠሩት የነበረ ሲሆን፣ይህም ህዝብ ይተገብርበት/ይገለገልበት የነበረው ከ3000 ዓ.ዓ ቀደም ብሎ እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ እንዲሁም በተለያዩ አካባቢዎችና ቦታዎች እንዲሁም በደቡብ ምስራቅ ኢሲያ ሀገራትም ተስፋፋተው እንደነበር የታሪክ ድርሳናት ያሳያሉው፡፡

በተመሳሳይ ሁኔታ የማሳጅ ህክምና በጥንታዊት ቻይና የረዥም ዓመት ታሪክ ያለው ነው፡፡ይህም የህክምና አይነት ከ2700 ዓ.ዓ አካባቢ ተግባራዊ ይደረግ እንደነበረ የታሪክ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ጥንታዊ ቻይናዊያን ማሳጅን ለህክምና አገልግሎትና ራስን ለማዝናናት ይጠቀሙበት ነበር፡፡ 

ወደ አህጉራችን አፍሪካ ስንመጣም ይህ የማሳጅ ህክምና አይነት በተለያዩ ሀገሮች ተግባራዊ መሆን ከጀመረ በሺ የሚቆጠሩ ዓመታት አስቆጥሯል፡ ፡ለምሳሌ በጥንታዊ ግብጽ የእራሳቸው የሆነ የማሳጅ አይነት ይጠቀሙ እንደነበር በፖፒረስ ላይ ተመዝግቦ ይገኛል፡፡የተለያዩ ተመራማሪዎች እንደሚገምቱት ሪፈሎኤሶሎጂክ/Reflexology/ የሚባለው ማሳጅ አይነት በግብጽ በ2500 ዓ.ዓ አካባቢ እንደተጀመረ ይገመታል፡፡ ይህን የማሳጅ አይነት የተወሰነ የሰውነት ክፍልን ብቻ የማሻል ስራ ላይ ያተኩራል፡፡(በሀገራችን ወጌሻ ጋር እንደምንሄደው)

 በተለያዩ ጊዜያት እንደሚታየው ማሳጅ የተለያዩ ጠቀሜታዎች እንዳለው ቢታወቅም ግን ከጊዜ ወደ ጊዜ እየወደቀ እየተነሳ የቆየበት ሁኔታ ስለነበረ አንዳንድ ባለሙያዎች በተለይም ከጥቂት መቶ ዓመታቶች በፊት ጠቀሜታው ወሳኝ እንደሆነ በመረዳት በ1600 ዓ.ም አከባቢ በምዕራባዊያን የህክምና ባለሙያዎች ድጋሚ ጠቀሜታውን በመገንዘብ ለአገልግሎት እንደ ገና ማዋል ተጀመረ፡ ፡ሆኖም ግን እስከ 19ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ ማሳጅ ከፍተኛ እውቅና በማግኘት በብዛት ጥቅም ላይ መዋል ጀመረ፡፡ አዲሱ ጥናት 

በቅርቡ ማክቤዝ ሚዲያ ኮሚኒኬሽን ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና ኤች አይ ቪ መቆጣጠሪያና መከላከያ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ወሲባዊ ንግድ የሚፈጸምባቸው ማሳጅ ቤቶች ላይ ትኩረት አድርጎ የተሰራው ጥናት ዋና ዓላማ ‹በሀገራችን መዲና በሆነችው አዲስ አበባ መጤ ባህሎችና ልማዳዊ ድርጊቶች በተለይም የተለየ ወሲባዊ ንግድ የሚፈጸምባቸው መታሻ/Massage parlor/ ማረፊያ ማሳጅ ቤቶች መስፋፋት እያስከተለ ያለውን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፤የስነተዋልዶ ጤና እና ስነልቦናዊ ተፅዕኖዎች እና ቀውሶች በሚመለከት ለችግሩ መነሻ ፣ አባባሽ ምክንያቶች እና የምክረ ሀሳብ/ የመፍትሄ ሃሳቦችን ማቅረብ እንደሆነ› ይገልፃል፡፡ 

መጤ ባህልና ልማዳዊ ድርጊቶች በወጣቶችና ሴቶች ላይ የሚያደርሷቸው ተጽዕኖዎች በርካታ  መሆናቸውን የሚጠቅሰው ጥናቱ በአፍሪካ ሀገራትም መጤ ባህል በአምራች ትውልዱ ላይ አሉታዊ ተጽኖ እያሳደረው እንደሆነ እንደ አብነትም ለምሳሌ፡ -በግብጽ ፤በሊቢያ(ከጎረቤት ሀገር)፤በሞሮኮ(ወንደኛ አዳሪነት..)፤በኬፕ ቬርዴ(የወሲብ ቱርዝም)እንዲሁም በናይጄሪያ(በፍተኛ ወሲብ ንግድ የሚተዳደሩ ሴቶችን ወደ ሌሎች ሀገሮች በመላክ የቀዳሚውን ድርሻ ከያዙት ሀገራት ውስጥ እንደሆኑ ያብራራል፡፡ 

ጥናቱ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ፤ ማለትም ከማሳጅ ማሰልጠኛ ተቋማት፣፤ ከማሳጅ ቤት ተጠቃሚዎች ፤ ከማሳጅ ቤት ሰራተኞች ጋር በርእሱ ዙሪያ ቃለ መጠይቅ በማድረግ የተሰራ ሲሆን ከዚህ `በተጨማሪም በአሳታፊ የአካል ምልከታ ማሳጅ ቤቶችን በመቃኘት መረጃዎች ተሰብስበዋል ይላል ፡፡ 

በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ አስር ክፍለ ከተማዎች የሚገኙ ሲሆን ከነዚህ ክፍለ ከተማዎች ማሳጅ የሚከናወንባቸው ቦሌ187 ፣ጉለሌ 5 ፣የካ 20፣ አዲስ ከተማ 9 ፣አቃቂ ቃሊቲ 0 ፣ቂርቆስ 77 ፣አራዳ 10 ፣ንፋስ ስልክ 30 ፣ልደታ 3፣ ኮልፌ 8 ሲሆኑ በጠቅላላው 349 (ሶስት መቶ አርባ ዘጠኝ ) ማሳጅ ቤቶች ከአዲስ አበባ ከንግድ እና ኢንዱስትሪ ቢሮ ፈቃድ አግኝተው በመስራት ላይ እንደሆኑ ጥናቱ ያመለክታል ፡፡ አብዛኛዎቹ የሚገኙትም ቦሌ አካካቢ በመሆኑ ቦሌ ክ/ከተማ ውስጥ ከሚገኙ 187 ማሳጅ ቤቶች ውስጥ 35 የሚሆኑ ማሳጅ ቤቶችን በመምረጥ ጥናቱ ተካሂዷል፡፡ የማሳጅ አገልግሎቱ የሚሰጥባቸውም ትላልቅ ህንፃዎች፣ ሰፋ ያለ ግቢ ያላቸው ቤቶች፣ አፓርታማዎችና በከተማዋ ዋና ዋና አካባቢዎች በሚገኙ ፎቆች ላይ የሚገኙ ቤቶች መሆናቸው ተረጋግጧል፡፡ ከእነዚህ ማሳጅ ቤቶች መካከል አብዛኞቹ ወደ ህገወጥ ተግባራት እየገቡ ሲሆን ጥናቱ እንደሚለው ለህገወጥ ማሳጅ ቤቶቹ መስፋፋት ተከታዮቹ ምክንያቶች በዋናነት ይነሳሉ፡- -

 ወሲባዊ ንግድ የሚፈጸምባቸው ማሳጅ ቤቶች ለባለቤቱና ወሲባዊ ንግድ ለሚትፈጽሙ ሴቶች ከፍተኛ ገንዘብ ስለሚያስገኝላቸው፣ 

- ተገልጋዮቹ የተሻለ ነጻነት እንዲሰማቸው ስለሚያደርግ፣ -

 ወሲባዊ ንግድ የሚፈጽሙ ሴቶች በሆቴልና በጎዳና ላይ ከሚያደርጉት ወሲባዊ ንግድ የማሳጅ ቤቱ በተሻለ ደህንነታቸው እንዲጠበቅ ስለሚያደርግላቸው፣ -

 ደላሎች ከዚህ ስራ የተሻለ ገንዘብ እያገኙበት ስለሆነ ስራውን እንዲስፋፋ አድርጎታል፣-

 ወሲባዊ ማሳጅ ቤቶች ተጠቃሚ የማህበረሰብ ክፍል እየጨመረ መምጣቱና ሌሎችም ምክንያቶች እንዳሉት ጥናቱ ደርሶበታል፡፡ 

ከገቢ አንፃርም በእነዚህ ማሳጅ ቤቶች ውስጥ መስራት ስለሚያስገኘው ገቢ በጥናቱ ውስጥ የተካተተ አንድ ሰራተኛ የሚከተለውን አስተያየት ሰጥቶ እናገኛለን፡፡ ‹በአሁኑ ሰዓት በመዲናችን ስትዟዟር በተለይም ደግሞ ቦሌ ክ/ከተማ ዞር ዞር እያልክ ብታይ ልክ እንደ ካፌ በየአካባቢው ወሲባዊ ንግድ የሚፈጸምባቸው ማሳጅ ቤቶች ተከፍተው ታገኛለህ፡፡ለዚህ ስራ በዋናነት ምክንያት የሚሆነው ደግሞ ለተጠቃሚው የሚሰጠው ተጨማሪ አገልግሎት (ወሲብ) ነው፡፡ለምሳሌ እኔ እሰራበት የነበረው ቤት ወደ ስድስት ማሳጅ የሚደረግባቸው ክፍሎች ነበሩት፡፡ከእነዚህ ክፍሎች ውስጥ ከምንሰራው ስድስት ወጣቶች ውስጥ እኔ ብቻ ነኝ ወንድ አምስቱ ሴቶች ናቸው፡፡እኛ ሁሌም ቀን ቀን ነው የምንሰራው፡፡ ማታ ፈረቃ የሚሰሩር በሙሉ ሴቶች ናቸው፡፡ እያንዳንዳችን በቀን ወደ 25 የሚጠጉ ደንበኞችን እናስተናግዳለን፡፡የማታ ፈረቃ ሰራተኞች ደግሞ ከ25 በላይ የሚሆን ሰው ያስተናግዳሉ፡፡በቀላሉ 50 ሰዎች ቢያስተናግዱ ለአንድ ሰው ዝቅተኛው ከ500 ብር እስከ 1200 ብር ያስከፍላሉ፡፡ በትንሹ 500 ብር ቢያስከፍሉ በአንድ ቀን 25,000 ብር ያገኛሉ ማለት ነው፤በወር ደግሞ 750,000 ብር ያገኛሉ፡፡ለሰራተኞችና ለአንዳንድ ወጪዎች 250,000 ብር ቢያወጡ ወደ 500,000 ብር ያገኛሉ፡፡በዚህም ምክንያት ማሳጅ ቤቶች እጅግ በፈጣን ሁኔታ እየተስፋፋ ይገኛሉ ፡፡› 

እንደዚህ ያለው ስራ በአብዛኛው ሀገር እጅግ በጣም የሚያዋጣ የስራ ዘርፍ ነው፡፡ እንደ ታይላንድ ያሉ ሀገሮች በወሲብ ንግድ በዓመት ውስጥ ወደ 4.3 ቢሊየን ዶላር ያገኛሉ ከወሲብ ንግድ ብቻ፡ ፡ይህም ብዙ ሰዎች በእንደዚህ አይነት ስራዎች ላይ እንዲሰማሩ ከሚያደርጓቸው ምክንያቶች ውስጥ አንዱ እንደሆነ በጥናቱ ተጠቅሷል፡፡ በተመሳሳይ መልኩም በአሜሪካ በተደረገ አንድ ጥናት መሰረት ወሲባዊ ንግድ ወደሚፈጸምባቸው ማሳጅ ቤቶች ስራ እንዲሰማሩ ምክንያት ከሆናቸው አንዱ ህጋዊ ማሳጅ ሲሰሩ የሚያገኙት ገንዘብ ዝቅተኛና ስራው አድካሚ ስለሆነ ወሲባዊ ንግድ ላይ ቢሰማሩ ግን በቀላሉ በዛ ያለ ገንዘብ ስለሚያገኙ ወደዚህ ስራ ይገባሉ ይላል ጥናቱ፡፡ 

በማህበራዊ ስነልቦና ባለሙያዎቹ አቶ በላይነህ ዘለለውና አቶ ዮሴፍ አህመድ የተደረገው ጥናት እንደሚያሳየው ወሲባዊ ንግድ የሚፈጸምባቸው ማሳጅ ቤቶች በሴቶችና በወጣቶች ላይ የማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ስነ-ልቦናዊ እና የስነ-ተዋልዶ ጤና ችግሮችን እንደሚያስከትሉ ያሳያል፡፡ በአንድ ማሳጅ ቤት ትሰራ የነበረች ወጣት ከስራው ጋር በተያያዘ ስለሚያጋጥማት ችግር ምንም አይነት ዋስትና እንደሌላት እንዲህ ስትል ታስረዳለች‹አገልግሎት ፈልጎ የሚመጣው ሰው በጣም የተለያየ ባህሪ ያለው ሰው ነው፡፡በዚህ ምክንያት ሁሉም የተለያየ ፍላጎት ስላለው፤አንዳንዱ ሰው ኮንዶም መጠቀም አይፈልግም፣ሌላው ደግሞ በፊንጢጣ የሚደረግ የግብረ ስጋ ግንኙነት ፈልጎ የሚመጣ አለ፡፡ ይህን ጊዜ ነው እንግዲህ ግጭት የሚፈጠረው፡ ፡ በተለይም ማታ የሚመጡት ወንዶች አብዛኛዎቹ መጠጥ ጠጥተው ስለሚመጡ የጠየቁትን ወሲብ አይነት እንቢ ካልኳቸው በጉልበት ሊፈጽሙብኝ ይሞክራሉ፤ አንዳንድ ከውጭ የመጡ ኢትዮጵያውያን (ዲያስፖራ) ወሲባዊ ፍላጎታቸው የሚረካው እኔን በማሰቃየት፣በመምታት፣በመንከስ ስለሆነ የተለያየ ጊዜ አደጋ ደርሶብኝ ያውቃል፡፡ ግን ይህንን ችግር ለማን ትናገረዋለህ ለባለቤቱ ብትነግረው ቢዝነሱ እንዳይበላሽበት ስለሚፈልግ ለፖሊስ እንድንናገር አይፈልግም እንዲሁም ደንበኞችን ላለማጣት ሲል ምንም እርምጃ አይወስድም፡፡እኔ ተጎድቼ ብቻ ነው የምቀረው ብናገር ሊያባረኝ ስለምችል ዝም ነው የምለው፡፡ › እነዚህ ሴቶች ምንም አይነት ጥቃት ቢደርስባቸው ለህግ አስከባሪ አካላት ሄደው አይናገሩም፤ ምክንያቱም የሚሰሩት ስራ በማህበረሰብ የተወገዘና እራሳቸው እራሱ የማያምኑበት ስለሆነ ጉዳት ደረሰብኝ ብለው ለፖሊስ ሪፖርት አያደርጉም፡

፡ይህ ደግሞ በእነሱ ላይ የሚደርሰውን የሀይል ጥቃት መጠን ለማወቅ አስቸጋሪ ያደርገዋል፡፡የመፍትሄ እርምጃ እንዳይወሰድ ደብቆ ያስቀረዋል ከዚህም አልፎ በሴ ቶ ቹ ላይ የሚደርሰውን አካላዊና ስነ- ልቦናዊ ጉዳት ተገንዝቦ ለመፍታት የሚደረገው ጥረት ያስተጓጉለዋል› ይላል፡፡ ይህ የስነ-ልቦና ችግር በተለይም እንደ ኢትዮጵያ ያሉ ሀይማኖታዊና ወግ አጥባቂ ማህበረሰብ ባለበት እነዚህ ወጣቶችና ሴቶች ከፍተኛ ለሆነ ለስነ-ልቦና ችግር ይጋለጣሉ፡፡በዚህም ምክንያት ወደ ጫትና ሺሻ ቤቶች በመሄድ ሱስ አስያዥ ዕፅና አልኮል በመጠቀም ችግራቸውን ለመርሳት ይሞክራሉ፡፡ በ2005 ዓ.ም በአዲስ አበባ አስተዳደር ሴቶች፣ ህጻናትና ወጣቶች ጉዳይ በተካሄደው ጥናት ሱስ አስያዥ ዕፆች(ጫት፣ሲጋራ፣ሀሺሽ፣ሺሻ፣ሄሮይን) እና የአልኮል መጠጦችን መጠቀም ችግር ከሁሉም በላይ የሆነ እና ለሌሎች ችግሮች ሁሉ መስፋፋት በመንስኤነቱ ትልቁን ድርሻ እንደሚይዝ በጥናቱ ላይ የተሳተፉ ሁሉም ግለሰቦች አረጋግጠዋል፡፡ ለአንደኛው ሱስ ተጋላጭ መሆን ለሌላኛው መንገድ እንደሚከፍትና ተያያዥነትም እንዳላቸው በጥናቱ ላይ የተሳተፉ ሰዎች ገልጸዋል፡፡ የመፍትሔ እርምጃዎች ጥናቱ የተለያዩ የመፍትሔ ርምጃዎችን በዝርዝር አስቀምጧል፡፡ 

ለማህበረሰቡ በቂ ግንዛቤ መፍጠር፣ ባለድርሻ አካላት በጋራ ተቀራርበው መስራት እንዳለባቸው፣ የተለያዩ የሀይማኖት ተቋማት ለተከታዮቻቸው ግንዛቤ መፍጠር እንዳለባቸው፣ ባለሀብቱ ኢንቨስትመንቱን ሀገር በሚጠቅም ነገር ላይ እንዲያውለው ተከታታይነት ያለው ትምህርት መሰጠት እንዳለበት፣ህጋዊ ማሳጅ ቤቶችን ማበረታታና ሌሎችም የመፍትሄ ሀሳቦች ተጨምረዋል፡፡ ባለድርሻ አካላት ተቀራርበው በመስራት እየተፈጠሩ ያሉትን ችግሮች ለመፍታት የጋራ እቅድ በማውጣት መስራት ይጠበቅባቸዋል፡፡ ኢኮኖሚያዊ፣ማህበራዊ፤ ስነ-ልቦናዊ የስነ ተዋልዶ ጤና ችግሮች ከወሲባዊ ንግድ ከሚካሄድባቸው ማሳጅ ቤቶች ጋር ያላቸው ትስስር ጠንካራና ቀጥተኛ መሆኑንና እነዚህ ችግሮች አምራች የሆኑትን ትውልዶች ለሀገራቸው ማበርከት የሚጠበቅባቸውን እንዳያበረክቱ እያደረጋቸው እንደሆነ ጥናቱ አሳይቶል፡፡ 

በስተመጨረሻም በመጤ ባህሎችና ልማዳዊ ድርጊቶች አሉታዊ ተፅዕኖ ምክንያት ላልተገቡ ባህሪያት እየተጋለጡ ያለውን ትውልድ ለመታደግ የተለያዩ እርምጃዎችን መወሰድ እንዳለበት ጥናቱ ጠቁሟል፡፡ የተለያዩ የሀይማኖት ተቋማት ሰለወሲባዊ ንግድ አስነዋሪነትና መጥፎ ገጽታዎች ለተከታዮቻቸው በማስተማር ወጣቶችና ሴቶች ከእንዲዚህ አይነት ተግባር እንዲቆጠብ ትምህርት ቢሰጡ፣ ባለሀብቱ ማህበረሰብን የሚጎዱ ተግባራት ላይ ኢንቨስት እንዳያደርግና ሴቶችንና ወጣቶችን ዘለቀታዊ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ዘርፎች ላይ እንዲሰማሩ ግንዛቤ መፍጠር ስራዎችን ማከናወን ይኖርበታል:: ለማሳጅ ቤት ባለቤትቶች ህጋዊ ሆነው ለህብረተሰብ ተገቢውን ማሳጅ አገልግሎት እንዲሰጡ በየጊዜ ትምህራታዊ ስልጠና መስጠት ያስፈልጋል :: በህጋዊነት እና የማሰጅን ስነምግባር ጠብቀው የሚሰሩ ማሳጅ ቤቶችን የተለየ ደጋፍ እና እረዳታ በደረግላቸው በቀላሉ ከገበያው የማይወጡ ይሆናሉ፡፡ ትምህርት ቤቶች አካባቢ የተከፈቱ እንዲሁም መኖሪያ አካባቢ የተከፈቱ የወሲብ ንግድ የሚፈጸምባቸው ማሳጅ ቤቶች በቶሎ ካካባቢው ቢነሱ እና በቦታው ለሌሎች የማህበረሰብን የእለት ተእለት እንቅስቃሴ የማያውክ ተግባረት የሚፈፀምባቸው በሆኑ ሀገርም ህብረተሰብንም የሚጠቅም ይሆናል :: ቤተሰብና ትምህርት ቤት በጋራ በመጣመር የልጆቻቸውንና የተማሪዎቻቸውን ውሎ በቅርብ ሆነው መከታተል አለባቸው፡፡ በተለያዩ ጊዜ የልጆቹን ሁኔታ ለመገምገም ወላጅና ትምህርት ቤት በጋራ በመዋያየት የሚታዩ ችግሮችን በእንጭጩ ለመቅጨት ይረዳቸዋል፡፡


Tuesday 27 January 2015

Serious criticizes the issue to EPRDF’s social, moral strategies sink such depth of immorality


Ethiopian Born Azarias Reda on TIME’s list of 12 New Faces of Black Leadership

++Reda, 29, was born in Ethiopia and moved to the U.S. to attend college. In 2012 he earned a Ph.D. in computer science engineering from the University of Michigan. Now he is a potentially pivotal player in U.S. politics, charged with improving the Republican National Committee’s database of American voters.

More related article about Azarias Reda from Wall Street Journal
“In Ethiopia, if you want to stay out of trouble, you don’t get involved in politics.” Ethiopian American Azarias Reda 
Leapfrogging the Democrats’ Tech Advantage
Wall Street Journal
Azarias Reda, a 28-year-old data evangelist, on giving the Republican voter operation a radical upgrade for the midterms.
Washington

No evidence exists that Francis Bacon made it to Ethiopia, but in a back room of the Republican National Committee building there is a lot of evidence that Azarias Reda absorbed one of the English philosopher’s more famous observations: scientia potentia est. The 28-year-old data evangelist is helping lead the effort to transform the GOP’s knowledge of voters into the power to win elections.
Republicans got thumped in the 2012 elections in no small part because of a voter-data failure. The Obama team crushed the Romney campaign and the RNC: on turnout, on targeting and in social media. Democrats are betting heavily that their operation will once again save the day—turning out enough voters in key states to save their Senate majority in November.
Mr. Reda, Ethiopian by birth, American by choice, was recruited by the RNC in November as its chief data officer. He and the nearly 50 data scientists and engineers he has recruited to an in-house tech incubator—Para Bellum Labs—are a mind-blowing sight at RNC headquarters. Hipsters in T-shirts and jeans wade through besuited politicians toward a digital room that sports rows of computers and dry-erase walls.
This room is where I met Mr. Reda last week and pointed out that Democrats are already ridiculing the Republicans’ big-data effort, claiming that there’s no way the GOP can catch the Obama turnout machine. The comment causes the otherwise serious young engineer to break out in a mischievous grin. “I don’t want to catch up to a presidential campaign from 2012,” he says, making 2012 sound like so last century. “What we’re doing here is what a tech startup would do in 2014. Data science has traveled a lot in just the past few years.”

The RNC line is that it intends to leapfrog Democrats in the technology of turnout, and a lot is riding on the claim. Twenty years ago the GOP created the first voter “file” on millions of Americans. Democrats spent years catching up, only to get outpaced again in 2004 by the Republican innovation of microtargeting, which allowed campaigns to contact and turn out subgroups of voters. The left then jumped forward in the run-up to 2008, creating a private outfit, Catalist, to serve as a data hub for the Democratic universe, harnessing the info of labor unions, activists, donors, campaigns. In 2012 the Obama campaign built on this by empowering its universe of volunteers with tools that let them use social media twitter and facebook to leverage this vast data store.
The GOP didn’t keep up. After 20 years and $150 million, the RNC by 2008 was sitting on the richest voter file on the planet but couldn’t mesh the information with its grass-roots network. In 2011 the party created its own outside entity, Data Trust, to serve as a movement-wide data clearing house. But the party failed to embrace the technology that would allow campaigns and volunteers to use the database. “It does nothing to have a big database with information just sitting there,” says Mr. Reda. “You need to get it out to people, present it in a way they can use it, derive insights from it.”
That’s Mr. Reda’s job. He moved to the U.S. from Ethiopia while in college, graduating from Sterling College in Kansas with degrees in computer science, applied mathematics and business. He followed that up by completing a Ph.D. in computer-science engineering from the University of Michigan in 2012. He did a tour at LinkedIn, and then moved to the startup world.
On a trip to Washington, he heard about the RNC’s data overhaul and was intrigued. “In Ethiopia, if you want to stay out of trouble, you don’t get involved in politics. But I’ve always been surprised by how well it works in the States,” he says. Technology is everywhere, he notes, yet “it hasn’t made it as much as it should in our political process. This was my way to work on something with real impact, and give something back to my country.” He’s one of a trio of tech gurus leading the RNC’s new data shop, including Chief Digital Officer Chuck DeFeo, and Chief Technology Officer (and former senior Facebook engineer) Andy Barkett.
Mr. Reda is charged with making the vast conservative voter file “actionable” and “accessible.” Actionable data, in Mr. Reda’s view, provides campaigns with knowledge of every voter. His team has focused on enriching its data—filling in thousands of data points on individual voters, from their age and geography and past election history, to what cars they buy, what services they subscribe to, what kind of house they live in.
Sophisticated data science and analytics will enable a campaign, says Mr. Reda, to determine individuals’ “political behavior, and what they are going to do.” Voters are categorized and sorted on all manner of attributes, thereby allowing campaigns to define specific “universes” of voters to target, and to apply the best techniques to persuade them. (Example: women between the ages of 35 and 50 who sat out the 2012 election but who are now worried about ObamaCare.) The files also assign scores to voters on such measures as party allegiance, propensity to vote and more.
The ultimate goal, says Mr. Reda, is to bank reliable voters in early and absentee voting, and then to quickly and continuously refocus resources on the next most persuadable set of voters.
Mr. Reda’s team takes measurements weekly in 22 states, calling tens of thousands of voters carefully selected as representative of the population. The team uses voters’ answers to specific questions to test its voter scores and models. The measurements have the added value of “tracking movement in voters’ views before they show up in the polls,” he says. This information is fed back to campaigns, allowing them to adjust their voter targets based on shifts in voter sentiment.
All this knowledge is useful, but the real power comes from “accessibility”—where the RNC thinks it is breaking the most new ground. In olden days—say, two years ago—the RNC data team fielded calls from campaigns and outside groups with specific requests for specific voter data sets. Fulfilling these requests took huge amounts of time, even as the info became quickly outdated.
The RNC innovation is what Mr. Reda calls a “political app store.” The tech team spent a year designing a common interface (think AAPL platform) that allows any outside partner to design its own apps to utilize the RNC voter data. “We have to support a bunch of Republican candidates across the country, and each campaign is different—each with different sets of problems to solve. And we have partners that are focused on yet entirely different things”—such as fundraising, or surveys, or voter engagement. “Our infrastructure allows them to be creative, to build their own technology that lets them use our data in the best way for them.”
Mr. Reda’s team developed the first app to demonstrate how it could work, but already the “people in our ecosystem are going far and beyond what we here would be able to build on the applications side.” Dozens of outsiders are working on or have already developed apps, and two were innovative enough that the RNC purchased and distributed them to all state campaigns.
Both are “walk” apps. Campaign volunteers load the app on their phone and use it to pull up a real-time list of targeted voters, complete with a GPS map, and details and scores about each target. Door-knockers use this information. “Hello, I know we agree on this set of issues,” Mr. Reda says, imitating an opening pitch.
Volunteers feed data that they get about the voter—answers to questions, or noting whether they’ve already voted—back into their phones, which immediately updates and enriches the RNC’s main voter file. Campaigns use that real-time data to update their targets, hone their messages and refine their Election Day get-out-the-vote strategy.
This real-time updating is meanwhile zipping across the conservative universe. Data Trust is legally allowed to work with any conservative organization as well as with the RNC. So the details that campaign volunteers collect on prospective voters are flowing through the RNC to Data Trust and to grass-roots canvassers—and vice versa. That data became immensely richer in August when Data Trust signed an info-sharing agreement with i360, the Koch brothers’ voter-data project.
The data are also flowing to Chuck DeFeo’s digital team, which is using voter information to refine its email and donation campaigns, and craft its social-media efforts. The Obama campaign’s use of social media to drive its base to the 2012 polls has become the stuff of legend.
But will the GOP be able to as effectively use social media as Democrats, given that many Republican base voters are older, and less tech-driven? Mr. Reda dismisses the point: “If you can reach someone on Twitter, reach someone on Facebook—great. The only thing that really matters is that you reach them.” His team has put a particular focus on collecting data on how best to contact each voter—Facebook, email, cellphone, text, home phone, home visit, work phone. He also argues that “it has been shown time and again in politics that the best contact is a personal one.” The RNC’s walk apps are geared toward enabling the GOP’s extensive volunteer and grass-roots networks to turn real contact into votes.
Republicans know that the Obama team retains its extensive voter-data file and techniques. The GOP’s big bet is that the Democratic data remain geared toward the party’s presidential nominee in 2012, while the GOP’s emphasis on flexibility and innovation will give it the midterm advantage.
Mr. Reda’s broader goal is creating a new “culture” at the RNC, a startup mentality that keeps the data shop nimble, flexible and constantly innovating. That’s the idea behind the open-source approach and Mr. Reda’s extensive recruitment. “I don’t view our competition” as an Obama campaign “that doesn’t even exist anymore,” he says. Instead the competition “is a startup desk in Austin, or in Silicon Valley, or here in D.C.”
Outsiders give the RNC credit for boldness, though complaints remain that the organization didn’t kick this project into high gear soon enough. The RNC wishes that the effort were further along but argues that its infrastructure—enhanced data, pinpoint targeting, voter scores, the walk app—was already good enough to win the Florida special election in Tampa in March, when David Jolly won in a congressional district that had voted for President Obama twice. “We were able to predict turnout. We were doing the absentee and early voter analysis, and firing off the right set of emails to the right set of contacts,” Mr. Reda says. “And it worked. It also gave us a chance to figure out how to scale this up to 22 states, and make it more secure, for this midterm.”
So is he confident enough to predict what will happen in the Senate? He flashes another smile: “Let’s just say I think the Senate is going our way. We’ll see Nov. 4.”
Ms. Strassel writes the Journal’s Potomac Watch column.

Sunday 25 January 2015

Julie Mehretu Awarded 2015 Medal of Arts by US State Department


The US Department of State has named Ethio-American artist Julie Mehretu, who is best known for her densely layered abstract paintings and prints, as a recipient of its 2015 Medal of Arts in recognition of her internationally acclaimed work and her impact in promoting cultural diplomacy. 
Julie is one of seven artists who is receiving the recognition for her “outstanding commitment and contributions to the Art in Embassies program and international cultural exchange” a State Department spokeswoman said.
“The 2015 winners are Xu Bing, Mark Bradford, Sam Gilliam, Maya Lin, Julie Mehretu, Pedro Reyes, and Kehinde Wiley. The biennial award began in 2013 and that year went to Cai Guo-Qiang, Jeff Koons, Shahzia Sikander, Kiki Smith, and Carrie Mae Weems.”
Julie, who lives and works in New York City, was the featured guest speaker at the 2014 American Artist Lecture Series in London this past September sponsored by the Art in Embassies program, Tate Modern and US Embassy London, which brings “the greatest living modern and contemporary American artists to the UK.”
Julie, who was also one of the Executive Producers of the film Difret, was born in Addis Ababa in 1970 and immigrated to the United States with her family in 1977. While best known for large-scale abstract paintings, Julie has experimented with prints since graduate school at the Rhode Island School of Design, where she was enrolled in the painting and printmaking program in the mid-1990s. 
Her exploration of printmaking began with etching. She has completed collaborative projects at professional printmaking studios across the US, among them Highpoint Editions in Minneapolis, Crown Point Press in San Francisco, and Derrière L’Etoile Studios and Burnet Editions in New York City.
Julie's works are held in the collection of the Museum of Modern Art. Although located in a private office building lobby, her 23' x 80' mural commissioned for the new Goldman Sachs tower in New York City (2010) is viewable from the sidewalk windows.
Julie is considered to be one of the leading contemporary artists in the United States, and has received numerous international recognition for her work including the American Art Award from the Whitney Museum of American Art and the prestigious MacArthur Fellow award.

Monday 19 January 2015

ካፒቴን አምሳሉ ጓሉ


በበረራ መማረክ የጀመርኩት ልጆች ሳለን አባቴ፣ እኔና እህቶቼን ወደ አየር ማረፊያ እየወሰደ አውሮፕላን ሲያርፍና ሲነሳ ያሳየን በነበረበት ወቅት ነው፡፡ አባቴ አውሮፕላኑን የሚያሳየን የአብራሪነት ፍላጎት እንዲቀሰቀስብን አስቦ አይመስለኝም፡፡ በእኔ ልብ ውስጥ የአብራሪነት ፍላጎት ያደረገው ግን በዚያ ጊዜ ነበር፡፡ ግዙፎቹ አውሮፕላኖች ሰማዩን እየሰነጠቁ ሲከንፉ በደስታ ተጥለቅልቀን መመልከታችን፣ አባታችንን ሳይከነክነው እንደማይቀር አስባለሁ፡፡ አባታችን ሁላችንም እንደየፍላጎታችን እንድንጓዝ ከማበረታታት ችላ ያለበት ጊዜ ባይኖርም፤ ያ የየሳምንቱ የአየር ማረፊያው ጉብኝታችን፣ እንዴት የበኩር ልጁ የእድሜ ልክ ሕይወትና ሙያ ሊሆን እንደቻለ አሁንም ድረስ ይገርመዋል፡፡
የተወለድኩት በ1969 ዓ.ም ባህርዳር ከተማ ነበር፡፡ አራት ልጆች ላፈሩት ወላጆቼ፤ የመጀመሪያ ልጅ ነኝ፡፡ ደህና ገቢ የነበራቸውን ወላጆቼን በአርአያነት እየተመለከትኩ ነው ያደግሁት፡፡ አባትና እናቴ በራሴ እንድተማመንና ህልሜን ለማሳካት እንድጣጣር ያበረታቱኝ ነበር፡፡ “ሴት በመሆንሽ ገደብሽ እዚህ ድረስ ነው” ብለውኝ አያውቁም፡፡
ያደግሁበት ማህበረሰብም፣ ለዛሬው ማንነቴ ትልቅ አስተዋጽኦ አበርክቷል፡፡ የአካባቢያችን ሰው ሁሉ እንደራሱ ልጅ ነበር የሚያየኝ፡፡ የእለት ተዕለት እድገቴን ከመከታተልም ባሻገር በትምህርቴ በርትቼ እንድገፋ ያበረታቱኝ ነበር፡፡
አብራሪ የመሆን ፍላጎቴን ሁሉም ያውቁ ስለነበር የማያደንቀኝ አልነበረም፡፡ ዘጠነኛ ክፍል ሳለሁ፣ ሁለት ታንዛኒያውያን (አንድ ወንድና አንድ ሴት) የበረራ ሰልጣኞች እኛ ሰፈር ይኖሩ ነበር፡፡ እናም በዩኒፎርማቸው ተማርኬ ፈዝዤ እመለከታቸው እንደነበር አስታውሳለሁ፡
የሶስት ዓመት ልጅ ሳለሁ፣ ቤተሰቦቼ ወደ አዲስ አበባ ስለመጡ፣ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቴን በአሳይ የህዝብ ትምህርት ቤት፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቴን ደግሞ በቦሌ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተከታተልኩ፡፡ በ1987 ዓ.ም ደግሞ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ፋኩልቲ ገብቼ፣ ሥነ-ህንፃ (አርኪቴክቸር) መማር ጀመርኩ፡፡
እንዲያም ሆኖ ግን የልጅነት ህልሜን አልዘነጋሁትም ነበር፡፡ የአንደኛ ዓመት ተማሪ ሳለሁ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአብራሪዎች ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት የመግቢያ ፈተናን ወስጄ ነበር፡፡ አብዛኞቹ ተፈታኞች በመጀመርያ ሙከራቸው ይወድቁ ነበር፡፡ እኔም ሳላልፍ ቀረሁ፡፡
በእርግጥ በመግቢያ ፈተናው መውደቄ ተስፋ አለመቁረጥንና የበለጠ መጣርን አስተምሮኛል፡፡ የሥነ - ህንፃ የመጨረሻ ዓመት ተማሪ ሳለሁ የመግቢያ ፈተናውን በድጋሚ ወሰድኩና አለፍኩ፡፡ ክፋቱ ግን አስቸጋሪ ሰዓት ላይ ሆነብኝ፡፡ የበረራ ሥልጠናው በሚጀመርበት በመጋቢት ወር 1992 ዓ.ም የዩኒቨርሲቲ ትምህርቴ የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ነበር፡፡
እናም ለዓመታት የለፋሁበትን ትምህርት ገደል እንደመክተት ሆነብኝ፡፡ የማታ ማታ ግን በሐምሌ 1992 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እንደተመረቅሁ ሥልጠናውን እንድጀምር ተፈቀደልኝ፡፡
ከሁለት ዓመት በላይ የወሰደውን ሥልጠና አጠናቅቄ በአብራሪነት የተመረቅሁት በህዳር 1994 ዓ.ም ሲሆን ለቀጣዮቹ ሰባት ዓመታት ተኩል በዘለቀው የሥራ ዘመኔም በረዳት አብራሪነት ለ4ሺ475 ሰዓታት አብርሬያለሁ፡፡
ከዚም ከተለያዩ ፈተናዎች፣ ምዘናዎችና ግምገማዎች በኋላ፣ እድገት ተሰጥቶኝ በዋና አብራሪነት (የካፒቴን) ሥልጠና ጀመርኩኝ፡፡ አስፈላጊውን የክህሎት ማጎልበቻ ሥልጠና እንዳጠናቀቅሁም ከመጀመሪያ በረራዬ ከሰባት ዓመት ተኩል በኋላ በ2002 ዓ.ም ካፒቴን ሆንኩኝ፡፡ ከዚያን ጊዜ ወዲህ ከአንድ ሺ በላይ ሰዓታት አብርሬአለሁ፡፡
ምንጭ፡ (“ተምሳሌት፡ ዕፁብ ድንቅ ኢትዮጵያውያን ሴቶች” ከተሰኘው አዲስ መፅሃፍ ላይ የተቀነጨበ፤ 2007 ዓ.ም)

Monday 12 January 2015

‹‹እናንተስ በምርጫ ትወርዱ ይሆን?›› ዲሞክራሲያዊ ለውጥ ላይ ልባችሁ ምን ይላል?

ወደ ጄኔራሉ የተወረወረው የአርቲስቷ ጥያቄ 
ብዙዎቹ ባለፉት ሁለት ቀናት ባዩትና በታዘቡት ነገር ተደምመዋል፡፡ የሰው ልጅ ሆኖ በዚህ በረሃ ውስጥ ሠፍሮ ለዚያውም ያኔ ሰው ባልነበረበትና አካባቢው የተለያዩ ሽፍቶች በሚንቀሳቀሱበት ሥፍራ፣ ከአሥር የማይበልጡ ሰዎች ባረጁና ጊዜያቸው ባለፈባቸው ጠመንጃዎች ትግሉ ከአርባ ዓመት በፊት በደደቢት ተጀምሮ ዛሬ የደረሰበትን ማመን ያቃታቸው ይመስል ነበር፡፡
ሕወሓት በተመሠረተበት ደደቢት በምትገኝ አንድ አነስተኛ የሐውልት ምልክት አካባቢ አቶ ስብሐት ነጋን ጨምሮ በአንጋፋ የሕወሓት (ኢሕአዴግ) አመራሮች በተደረገ ገለጻ የአካባቢውን አስቸጋሪነትና ሙቀት አይተዋል፡፡ እዚህ ቦታ ላይ የታጋዮች ሕይወት ምን ይመስል እንደነበር ያኔ የ30 ዓመት ወጣት የነበሩት ወያናይ ካህሳይ በቀጥታ ትዝታቸውን አካፍለዋል፡፡ ወያናይ ካህሳይ የዱር አራዊት እያደኑ ይመግቧቸው እንደነበር፣ ምግብ ማብሰያውም ሆነ እንደ ሰሀን የሚያገለግለውም ድንጋይ እንደነበር የተናገሩት ለጐብኚዎቹ በጭንቅላታቸው ውስጥ እያቃጨለ ውሏል፡፡ 
እሱም ብቻ አይደለም፡፡ ከደደቢት መልስ በሁለተኛው ቀን ከሽረ እንደሥላሴ በተደረገው የግማሽ ቀን አስቸጋሪ ጉዞ ደጀን በተባለው አካባቢ የሚገኘው ‹‹ሚስጥራዊ›› ዋሻ መመልከትም የሚታመን አልነበረም፡፡ ይህ ተደጋጋሚ በደርግ አውሮፕላኖች ድብደባ ተደርጐበት ምንም ጉዳት ሳይደርስበት፣ አንድም ታጋይ አደጋ ሳያጋጥም ድርጅቱን የታደገ ዋሻ፣ በውስጡ ጽሕፈት ቤቶችም ያካተተ ሲሆን፣ የዋሻው የመጀመሪያ ክፍል አነስተኛ የስታዲየም ቅርፅ ኖሮት ለስብሰባ እንዲመች ተደርጎ የተሠራ ነው፡፡ ድርጅቱ ለመጨረሻ ጊዜ ከውድቀት ራሱን የታደገበትና አዳዲስ የፖለቲካ አስተሳሰብ የቀረፀበት እንዲሁም ከፍተኛ የእርስ በርስ ግምገማ የተደረገበት ሥፍራ መሆኑም ይነገራል፡፡ እዚያ ለመድረስ አስቸጋሪ ቢሆንም ከጥቂቶች በስተቀር በዕድሜ የገፉ የሥነ ሥርዓቱ ተሳታፊዎች ሳይቀሩ ገደሉን አልፈው ሄደው ተደግፈው ለማየት ችለዋል፡፡ 
ወደ አካባቢው ለመድረስ ከትግል የማይተናነስ ፅናት የሚጠይቅ ነበር፡፡ የፕሮግራሙ መጨናነቅ ታክሎበት ብዙዎችን ያማረረ ረጅም ጉዞ ነበር፡፡ ብዙዎቹ ሥፍራውን አይተው ከተመለሱ በኋላ ግን በትዝታቸው ውስጥ የሚቀረው ጥቂቱ ብቻ ይመስላል፡፡ በየአካባቢው ሕዝቡ ባሳያቸው ከፍተኛ ፍቅርና በእነዚህ ሚስጥራዊ ሥፍራዎች ባዩዋቸው ታሪካዊ ሁነቶች ባይመሰጡ፣ ምናልባት ወደ መጣንበት መልሱን ማለታቸው የሚቀር አይመስልም፡፡ 
በሕይወት ከሌሉት የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ በስተቀር የሕወሓት መሥራችና አንጋፋ ሰዎች መካከል አብዛኞቹ ጐብኚዎቹን አጅበው ታሪካቸውን ሲነግሩ ሲያስነግሩና ሲያሳዩ ሰነባብተዋል፡፡ አብዛኛው በመኪና ጉዞ የሚያልፈው ጊዜ በፈጠረባቸው ድካምና መሰላቸት የሚታይባቸው ጐብኚዎች በሦስተኛው ቀን ካደሩበት ከሽረ እንደሥላሴ እምብዛም ርቀት ሳይኖረው አንድ ታሪካዊ ቦታ ለማየት ተንቀሳቅሰዋል፡፡ የደርግ መንግሥት 604ኛ ኮር የተደመሰሰበት ሥፍራ ነው፡፡ አንዳንድ ጸሐፊዎች እንደገለጹት፣ ሕወሓትን ከመላ ትግራይ ጠራርጐ ለማጥፋት በአራትና በአምስት ግንባሮች ከኤርትራም አቅጣጫ ሳይቀር የዘመተበትና በመጨረሻም ሕወሓት በደርግ ወታደሮች ላይ የውጊያ የበላይነቱን የተቆጣጠረበት ‹‹የሞት ሽረት›› ውጊያ የተደረገበት ሥፍራ ነበር፡፡ ከዚህ አንድ ተራራ ጫፍ በመሆን የሽረ ከተማን ሙሉ ማየት በሚቻለው ቦታ ላይ አጭር ገለጻ ከተደረገላቸው በኋላ ስብሰባ ወደተዘጋጀበት አዳራሽ ነበር ያመሩት፡፡ 
ቀደም ብሎ ደደቢት ላይ በተደረገው ውይይት አቶ ስብሐት ነጋ፣ አቶ ዓባይ ፀሐዬና አምባሳደር ሥዩም መስፍን በወያናይ ካህሳይ ታጅበው ስለሕወሓት አመሠራረት፣ ሕወሓት ከሌሎች ድርጅቶች ጋር ስለነበረው ግንኙነት፣ እንዲሁም የሕወሓት ፖለቲካዊ አስተሳሰብና አኅጽሮት ጋር በተያያዘ መድረክ ላይ ተቀምጠው እየተጋገዙ ነበር ገለጻ ያደረጉት፡፡ 
ከዚህ በተቃራኒ በአሁኑ ወቅት የአካባቢው ወታደራዊ ዕዝ መቀመጫ በሆነው በዚሁ ሥፍራ ግን አንድ ሰው ብቻቸውን ተቀምጠው ይታያሉ፡፡ ቀስ በቀስም ከፊት ያሉት ወንበሮች የትግራይ የቀድሞ ፕሬዚዳንትን አቶ ፀጋይ በርሃንና የትግራይ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ኪሮስ ቢተውን ጨምሮ አቦይ ስብሐት ነጋ፣ አምባሳደር ሥዩም መስፍን፣ አቶ ዓባይ ፀሐዬ፣ አቶ አዲሱ ለገሰ፣ አቶ በረከት ስምኦን እንዲሁም አቶ ካሱ ኢላላ የፊት ወንበሮች በረድፍ ተቀምጠዋል፡፡ 
‹‹መደመር አልቻልንም ነበር››
ከመድረኩ በስተጀርባ ከነበሩት በርከት ያሉ የቀድሞው የጠቅላይ ሚኒስትር መለስን ምሥሎች ከያዘው ሸራ ውጪ ብቻቸውን ተቀምጠው በእጅ የተጻፉ በርከት ያሉ ማስታወሻ የያዙ ወረቀቶች የሚያገላብጡ የቀድሞ ታጋይ፣ የአሁኑ የኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ጠቅላይ ኤታማዥር ሹም ጄኔራል ሳሞራ ዩኑስ ነበሩ፡፡ 
ያቀረቡት ጽሑፍ ጠቅለል ተደርጐ ሲቀርብ ድርጅቱ ለአሥር ዓመታት ያህል የሽምቅ ውጊያ ላይ የነበረ በመሆኑ ‹‹መደመር አልቻልንም ነበር›› የሚለውን ነው፡፡ ይኼውም አንድ ቦታ ላይ አጥቅተው ሲመለሱ ቦታው በደርግ ይዞታ ሥር መልሶ የሚወድቅበት አጋጣሚ ይበዛ ነበር ከሚል ነው፡፡ ይኼ ታሪክ የተቀየረው ወታደራዊ እንቅስቃሴው እንደ ሳይንስ ተቆጥሮ በደጀና ላይ ከፍተኛ ጥናት ቀርቦ ውይይት ከተደረገበት በኋላ እንደነበር አስረድተዋል፡፡ የዚሁ ዋነኛ የትግል መገለጫም የ604ኛ ኮር መደምሰስ ነበር፡፡ 
አንጋፋ ፖለቲከኞቹ ምንም ዓይነት የፕሮቶኮል አለባበስ ያልነበራቸው ሲሆን፣ ‹‹ሻዕቢያ ጉድጓድ መቆፈር ይችላል፣ እኛ ደግሞ ከጉድጓድ አውጥተን መቅበር እንችላለን፤›› በሚለው ንግግራቸው በስፋት የሚታወቁት ጄኔራል ሳሞራ ዩኑስ ደግሞ ቀለል ያለ ሹራብ ጣል አድርገው ምንም ዓይነት ወታደራዊ ፕሮቶኮል አልበራቸውም፡፡
አቀራረባቸውም ቢሆን ለብዙዎች የተመቸና የጉብኝቱ ተሳታፊዎች የሕወሓት ወታደራዊ ሥልትና ታክቲክን በቀላል መንገድ እንዲረዱ የረዳ ነበር፡፡ በሦስት ምዕራፍ ከፋፍለው ያቀረቡት ይኼው የሕወሓት የትግል ታክቲክ ከ500 ሺሕ በላይ ጦር የነበረውና በአፍሪካ ወደር ያልነበረው የደርግ ጦር ሠራዊትን ያሸነፈበት ‹‹ሕዝባዊና ወታደራዊ›› ሳይንስ ካብራሩ በኋላ አንዳንዶቹ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ የመጀመሪያው ጠያቂ አርቲስት አበበ ባልቻ ሲሆን፣ በዚህ የ604ኛ ኮር ጦርነት የሻዕቢያ ሚና ምን ነበር የተነገረው? ወታደራዊ ፍፃሜዎችስ ምን ያህል በጽሑፍና በምሥል ተሰንደዋል? የሚል ነበር፡፡ ጄኔራሉ ሲመልሱ በነበራቸው በወታደራዊ ትብብሩ መሠረት ‹‹የሕወሓት ታጋዮች በሳህል ተራሮች ጦርነት እንደተሳተፉ ሁሉ ሻዕቢያም በትንሹም ቢሆን ተሳትፏል፤›› ብለዋል፡፡ እነሱ በሚያወሩት ደረጃም ባይሆን፡፡  
አቶ ሳምሶን ማሞ አስተያየትም ጥያቄም አቅርቧል፡፡ ‹‹ባለፉት 23 ዓመታት ያየሁት የደርግ ወታደሮች በሚጽፉት ድርሰት ምክንያት እነሱ አሸናፊ መስለው እስከመታየት ደርሷል፡፡ ምናልባትም ትንሽ ቆይተን አቶ ለገሰ አስፋው ‘እኔና ሐውዜን’ የሚል መጽሐፍ ሊጽፉ ይችላሉ፤›› በማለት ታዳሚዎችን ፈገግ አሰኝቷል፡፡ ታሪካቸውን እንዲጽፉ ወታደራዊ ሚስጥሮቻቸውን ሳይቀር ለጸሐፊዎች ክፍት እንዲያደርጉ አርቲስቶችን በመወከል ነበር የተናገረው፡፡ ‹‹ይኼ ታሪክ የትግራይ ሕዝብ ብቻም አይደለም፡፡ የኢትዮጵያ ታሪክ ሆኗል፡፡ መብታችን ነው ፍቀዱልን እንጻፈው፡፡ ሥርዓቱ እንዲቀጥል እንፈልጋለን፡፡ ከፋም ለማም የኢትዮጵያ ሕዝብ ከሥርዓቱ ተጠቃሚ ነው፤›› ሲል በታዳሚዎቹ ከፍተኛ የድጋፍ ጭብጨባ ታጅቧል፡፡
‹‹ማንንም ለማዳን ብዬ ሳይሆን ለራሴ ስል ነው፡፡ አገሬን አሳልፌ አልሰጥም፡፡ የአገር መፍረስ ማለት እነዚህ ኃይሎች የራሳቸውን የፈጠራ ታሪክ እየጻፉ የሕዝቡን አስተሳሰብ መቀየር ሲችሉ ብቻ ነው›› ሲል አስተያየቱን ቋጭቷል፡፡ 
‹‹እናንተን የሚተካ አዲስ መሪ››
በመጨረሻ ዕድሉ የተሰጣት አርቲስት አስቴር በዳኔ ከተቀመጠችበት ወደፊት ወጥታ ማይኩን ስትጨብጥ ፍርኃት ቢጤ እንደወረራት ከመጀመሪያው ያስታውቃል፡፡ ‹‹በጣም ነው የሚያስፈራው፤›› በማለት የጀመረችውን አስተያየቷን የያዘችውን ማስታወሻ እያነበበች አስተያየት መስጠት ቀጠለች፡፡ 
‹‹ይህንን ዕድል ተመቻችቶልን በቴሌቪዥን ስናየው የኖርነው ታሪክ ለማየት ስለቻለን እጅግ ከፍተኛ ደስታ ተሰምቶኛል፡፡ በፊት የነበረኝ ያልተጨበጠ አመለካከት በመረጃ የተደገፈ ሆኗል፤›› በማለት ሐሳቧን ቀጠለች፡፡ ‹‹እውነትን መናገር እወዳለሁ፡፡ የሐሳብ ነፃነትም አለ፡፡ በእርግጥ የፖለቲካ ሰው አይደለሁም፤›› በማለት ታዳሚዎችን ፈገግ ያሰኘች ሲሆን፣ በሒደትም የፍርኃቷ መጠን እየቀነስ የመጣ ይመስላል፡፡ 
‹‹ዛሬ ባልናገረው የሚቆጨኝ የተከፈለው መስዋዕትነት እጅግ በጣም ከባድ እንደነበር ግልጽ ነው፡፡ የሕወሓት ታሪክ አንድ የኢትዮጵያ ታሪክ ነው፡፡ በጆሮ ስሰማው ደርግ ተደምስሶ ታጋይ እንዲህ ሆኖ ሲባል ከሁለቱም ወገን የተሰዉት በአጠቃላይ የኢትዮጵያ ልጆች ናቸው፡፡ የሞቱት፣ እግራቸው የተቆረጠ፣ ዓይናቸው የጠፋ ስላሉ ለሁለቱም ‹ጠላት› የሚለው ቃል ተገቢ አይመስለኝም፡፡ የወንድማማቾች ደም በመፍሰሱ ቤተሰቦቻቸው ዘንድ ሄደን ስናይ ልብ የሚሰብር ነው፡፡ ነገር ግን ይህ የጦርነትና የትግል ታሪክ ዘመኑ የፈጠረው ነው፡፡ በወቅቱ መንግሥታዊ ለውጥ ለማምጣት የትጥቅ ትግሉ አማራጭ አልነበረውም፡፡ አሁንስ?›› አርቲስት አስቴር ትንፋሿን ዋጥ በማድረግ ቀጠለች፡፡ 
‹‹የትግሉ ዋና ሐሳብ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት በአገሪቱ ለማምጣት ነው፡፡ የመንግሥትም ሆነ የሥርዓት ለውጥ በጦርነት ሳይሆን በዲሞክራሲ እንዲሆን ነበር ያ ሁሉ ከባድ መስዋዕትነት የተከፈለው፡፡ አሁን ላይ ሲታሰብ የሚመጣው ግንቦት ላይ 24 ዓመት የሚሆነው ሥልጣን ላይ ያለው አንድ ፓርቲ ነው፡፡ ዲሞክራሲያዊ ለውጥ ላይ ልባችሁ ምን ይላል? ያኔ ለሥልጣን ሳይሆን ለሕዝብ ስትታገሉ በጦርነት ሳይሆን በዲሞክራሲ ለውጥ እንዲደረግ ነበር፡፡ አይለደም?›› በማለት ጠየቀች፡፡
‹‹በእርግጥ የድሮን አስተሳሰብ መናፈቅ አዲስ አስተሳሰብ ለመቀበል ይከብዳል፡፡ አሁን ዝም ብዬ ሳስበው ራሱ ተቃዋሚ የሚለው ቃል ራሱ ጥሩ አይደለም፡፡ ተፎካካሪ ቢባል፡፡ አዲስ አስተሳሰብና ፍልስፍና ያለው ተተኪ መሪ ሊፈጠር አይችልም የሚል አቋም ነው ያላችሁ?›› በማለት ሐሳቧን ያልቋጨችው አርቲስት አስቴር፣ ሐሳቧ በብዙዎች ተጠብቆ የነበረ አይመስልም፡፡ ‹‹አመሰግናለሁ›› የሚለው የመጨረሻውን ቃል እስክትናገር ከአጠገቧ የተቀመጡ ኢትዮጵያን እየመሩ ያሉት አንጋፋ ታጋዮች ጥያቄው እስኪያልቅ የተጨነቁ ይመስላል፡፡ እርስ በርስ አየት ተደራርገው የተለዋወጡት ፈገግታ ጥያቄውን የጠበቁት እንዳልሆነ ያሳብቃል፡፡ በእርግጥም በምርጫ ዋዜማ ሆነው ለጥያቄው ምን ተብሎ ምላሽ እንደሚሰጥ ሳያስጨንቃቸው አልቀረም፡፡
‹‹እውነት መናገር እውዳለሁ›› በሚል የጀመረችው ፍርኃት እየፈጠረባትም ቢመስል የመጨረሻ ማጠናቀቂያ ሐሳቧ እንዲህ ነበር የሚለው፡፡ ‹‹ምክንያቱም እግዚአብሔር ምስክሬ ነው፡፡ ቁርጠኛ የሆነ ታሪክ ያፈራ በኢትዮጵያ አይደለም በዓለም የሚደነቅ የትግል ታሪክ ነው ያላችሁ፡፡ ‘So, next time’ ምን ያህል አዲስ ታሪክ አዲስ አስተሳሰብ በዲሞክራሲያዊ ምርጫ ተለውጦ እናያለን?›› የሚለው ፈራ ተባ እያለች የጨረሰችውን ጥያቄ ‹‹ውርድ ከራሴ›› ይመስል ድምጿ እየተቆራረጠ ‹‹አመሰግናለሁ›› ብላ፣ ‹‹እናንተስ በምርጫ ትወርዱ ይሆን?›› ብላ ነበር ጥያቄዋን የቋጨችው፡፡
አቶ በረከት ስምኦን ሁለት እጆቻቸውን ወደፊት ወስደው እንደማፍተልተል ሲያደርጉ፣ ሌሎች ብዙዎቹ አንጋፋ አመራሮች በግርምት ጉንጫቸውን ደገፍ አድርገው ይዘው ታይተዋል፡፡ 
ጄኔራል ሳሞራ መልሳቸውን በመጨረሻውና ጠንከር ባለው ጥያቄ ላይ የጀመሩ ሲሆን፣ ‹‹ተቃዋሚ የሚለው ችግር ያለው አይመስለኝም፡፡ አንቺ ያመጣሽውም ቢሆን የሚጠላ አይደለም፡፡ ተቃዋሚ የሚጠላ ድርጅት ያለ አይመስለኝም፡፡ ኢሕአዴግ ተቃዋሚ የሚጠላ ቢሆን ኖሮ እንደ ሻዕቢያ በሩን መዝጋት ይችል ነበር፤›› ብለዋል፡፡ 
የኤርትራ መንግሥት የሚጠቀመውን ‹‹ሓደ ልቢ፣ ሓደ ሥርዓት፣ ሓደ ሕዝቢ›› የሚለውን አገላለጽ ተርጉመው ‹‹አንድ ልብ፣ አንድ ሕዝብ፣ አንድ ሥርዓት›› የሚለውን አስቀምጠው እጆቻቸውን እያወናጨፉ፣ ‹‹ኢሕአዴግ  ተቃዋሚ የማይቀበል አመለካከትና አስተሳሰብ ቢኖረው ኖሮ የዲሞክራሲ መንገድም አይታይም ነበር፡፡ ጋዜጦችን መዝጋት ይቻላል፡፡ የኢሕአዴግ ዓላማ ራሱ ይኼ አይመስለኝም፤›› በማለት ወደ ተቃዋሚዎች ጣታቸውን ቀስረዋል፡፡ 
‹‹አንድ ነገር ልጨምር፡፡ በአስተሳሰብ ወይም በፖሊሲ የሚቃወም ተቃዋሚ የሚጠላ አይመስለኝም፡፡ የሚፈለግ ይመስለኛል፡፡ እኛ ጋ ያለው ተቃዋሚ ግን ብሔራዊ ጥቅምን ለሌላ አሳልፎ እየሰጠ የሚቃወም ተቃዋሚ ነው፤›› የሚለው ንግግራቸው በከፍተኛ ጭብጨባ የታጀበ ነበር፡፡ 
‹‹አገሩን ለሌላ እየሰጠ የሚቃወም ተቃዋሚ ለምሳሌ የዚህች አገር መከላከያ ቢበተን ደስ ይለዋል፡፡ እንዲበተንም የሚሠራ ነው፡፡ አገር እየተተራመሰች እንድትኖር የሚፈልግ ተቃዋሚ ተቃዋሚ አይደለም፡፡ አንቺ ባልሽው በዚህ እስማማለሁ፡፡ ተቃዋሚ እንደዚህ ከሆነ፡፡ ለማንኛውም እኔ ምድብተኛ ወታደር ነኝ፤›› በማለት ሐሳባቸውን ቋጭተው በፈገግታ የውይይቱ ተሳታፊዎችን ተሰናብተዋል፡፡ በሌሎች ጥያቄዎች ላይ ምልልሱ ቢቀጥልም፣ ነገር ግን ሌሎች የፖለቲካ አመራሮች በዚሁ ጉዳይ ላይ አስተያየት ሳይሰጡ ቀርተዋል፡፡  

Friday 2 January 2015

Ethiopia’s Capital is now the Home of the Largest Houses of Prostitution in Africa

OFFICE TO MONITOR AND COMBAT TRAFFICKING IN PERSONS

Ethiopia is a source and, to a lesser extent, destination and transit country for men, women, and children who are subjected to forced labor and sex trafficking. Girls from Ethiopia’s rural areas are exploited in domestic servitude and, less frequently, prostitution within the country, while boys are subjected to forced labor in traditional weaving, herding, guarding, and street vending. The central market in Addis Ababa is home to the largest collection of brothels in Africa, with girls as young as 8-years-old in prostitution in these establishments. Ethiopian girls are forced into domestic servitude and prostitution outside of Ethiopia, primarily in Djibouti, South Sudan, and in the Middle East. Ethiopian boys are subjected to forced labor in Djibouti as shop assistants, errand boys, domestic workers, thieves, and street beggars. Young people from Ethiopia’s vast rural areas are aggressively recruited with promises of a better life and are likely targeted because of the demand for cheap domestic labor in the Middle East.

Many young Ethiopians transit through Djibouti, Egypt, Somalia, Sudan, or Yemen as they emigrate seeking work in the Middle East; some become stranded and exploited in these transit countries, and are subjected to detention, extortion, and severe abuses—some of which include forced labor and sex trafficking—while en route to their final destinations. Young women are subjected to domestic servitude throughout the Middle East, as well as in Sudan and South Sudan. Many Ethiopian women working in domestic service in the Middle East face severe abuses, including physical and sexual assault, denial of salary, sleep deprivation, withholding of passports, confinement, and even murder. Ethiopian women are sometimes exploited in the sex trade after migrating for labor purposes—particularly in brothels, mining camps, and near oil fields in Sudan and South Sudan—or after fleeing abusive employers in the Middle East. Low-skilled Ethiopian men and boys migrate to Saudi Arabia, the Gulf States, and other African nations, where some are subjected to forced labor. In October 2013, the Ethiopian government banned overseas labor recruitment. Preceding the ban, Ministry of Labor and Social Affairs (MOLSA) officials reported that up to 1,500 Ethiopians departed daily as part of the legal migration process. Officials estimated this likely represented only 30 to 40 percent of those migrating for work; the remaining 60 to 70 percent were smuggled with the facilitation of illegal brokers. Brokers serve as the primary recruiters in rural areas. Over 400 employment agencies were licensed to recruit Ethiopians for work abroad; however, government officials acknowledged many to be involved in both legal and illegal recruitment, leading to the government’s ban on labor export. Following the ban, irregular labor migration through Sudan is believed to have increased. Eritreans residing in Ethiopia-based refugee camps, some of whom voluntarily migrate out of the camps, and others who are lured or abducted from the camps, face situations of human trafficking in Sudan and Egypt’s Sinai Peninsula.

Since November 2013, the Saudi Arabian government has deported over 163,000 Ethiopians, including over 94,000 men working mostly in the construction sector and over 8,000 children working in cattle herding and domestic service; international organizations and Ethiopian officials believe thousands were likely trafficking victims. Many migrants reported not having repaid debts to those who smuggled them to Saudi Arabia, rendering some of them at risk for re-trafficking.

The Government of Ethiopia does not fully comply with the minimum standards for the elimination of trafficking; however, it is making significant efforts to do so. The Federal High Court convicted 106 traffickers and worked with international partners to shelter and provide emergency care to trafficking victims. In 2013, following an influx of trafficking victims returning to Ethiopia, the government recognized problems with its oversight of Ethiopian-based employment agencies, which were failing to protect workers sent overseas. In response, the government temporarily banned labor recruitment and began to revise the relevant employment proclamation to ensure improved oversight of these agencies and better protection of its citizens while working abroad. The government facilitated the return of thousands of Ethiopians, including many likely trafficking victims, deported from Saudi Arabia and elsewhere during the reporting period, and coordinated with NGOs and international organizations to provide services to the returning migrants. The government relied on NGOs to provide direct assistance to both internal and transnational trafficking victims and did not provide financial or in-kind support to such organizations. The government did not deploy labor attachés or improve the availability of protective services offered by its overseas diplomatic missions. The absence of government-organized trainings in 2013 was a concern. The government also did not effectively address child prostitution and other forms of internal trafficking through law enforcement, protection, or prevention efforts. It did not report on the number of victims it identified in 2013.

Recommendations for Ethiopia:

Complete amendments to the employment exchange proclamation to ensure penalization of illegal recruitment and improved oversight of overseas recruitment agencies; strengthen criminal code penalties for sex trafficking and amend criminal code Articles 597 and 635 to include a clear definition of human trafficking that includes the trafficking of male victims and enhanced penalties that are commensurate with other serious crimes; enhance judicial understanding of trafficking and improve the investigative capacity of police throughout the country to allow for more prosecutions of internal child trafficking offenses; increase the use of Articles 596, 597, and 635 to prosecute cases of labor and sex trafficking; improve screening procedures in the distribution of national identification cards and passports to ensure children are not fraudulently acquiring these; allocate appropriate funding for the deployment of labor attachés to overseas diplomatic missions; institute regular trafficking awareness training for diplomats posted abroad, as well as labor officials who validate employment contracts or regulate employment agencies, to ensure the protection of Ethiopians seeking work or employed overseas; incorporate information on human trafficking and labor rights in Middle Eastern and other countries into pre-departure training provided to migrant workers; engage Middle Eastern governments on improving protections for Ethiopian workers; partner with local NGOs to increase the level of services available to trafficking victims returning from overseas, including allocating funding to enable the continuous operation of either a government or NGO-run shelter; improve the productivity of the national anti-trafficking taskforce; and launch a national anti-trafficking awareness campaign at the local and regional levels.

Prosecution

The Government of Ethiopia maintained its anti-trafficking law enforcement efforts during the reporting period, but its efforts continued to focus wholly on transnational trafficking, with little evidence that the government investigated or prosecuted sex trafficking or internal labor trafficking cases. Ethiopia prohibits sex and labor trafficking through criminal code Articles 596 (Enslavement), 597 (Trafficking in Women and Children), 635 (Traffic in Women and Minors), and 636 (Aggravation to the Crime). Article 635, which prohibits sex trafficking, prescribes punishments not exceeding five years’ imprisonment, penalties which are sufficiently stringent, though not commensurate with penalties prescribed for other serious crimes, such as rape. Articles 596 and 597 outlaw slavery and labor trafficking and prescribe punishments of five to 20 years’ imprisonment, penalties which are sufficiently stringent. Articles 597 and 635, however, lack a clear definition of human trafficking, do not include coverage for crimes committed against adult male victims, and have rarely been used to prosecute trafficking offenses. Instead, Articles 598 (Unlawful Sending of Ethiopians to Work Abroad) and 571 (Endangering the Life of Another) are regularly used to prosecute cases of transnational labor trafficking. The absence of a clear legal definition of human trafficking in law impeded the Ethiopian Federal Police’s (EFP) and Ministry of Justice’s ability to investigate and prosecute trafficking cases effectively. Officials began drafting amendments to the Employment Exchange Services Proclamation No. 632/2009, which governs the work of approximately 400 licensed labor recruitment agencies; planned amendments will prohibit illegal recruitment and improve oversight of recruitment agencies.

During the reporting period, the EFP’s Human Trafficking and Narcotics Section, located within the Organized Crime Investigation Unit, investigated 135 suspected trafficking cases—compared to 133 cases in the previous reporting period. The federal government reported prosecuting 137 cases involving an unknown number of defendants relating to transnational labor trafficking under Article 598; of these cases, the Federal High Court convicted 106 labor traffickers—compared to 100 labor traffickers convicted in the previous reporting period. Officials indicated that these prosecutions included cases against private employment agencies and brokers, but did not provide details on these cases or the average length of applied sentences. Between June and July 2013, courts in the Southern Nations, Nationalities, and Peoples Region (SNNPR) reportedly heard 267 cases involving illegal smugglers and brokers. In addition, in Gamo Gofa, a zone within SNNPR, the zonal court convicted six traffickers in 2013—the first convictions in that area’s history. The EFP investigated allegations of complicity in trafficking-related crimes involving staff at several foreign diplomatic missions in Addis Ababa; the EFP arrested several staff at these missions.

In 2013, the government did not initiate any sex trafficking prosecutions, including for child prostitution. It also did not demonstrate adequate efforts to investigate and prosecute internal trafficking crimes or support and empower regional authorities to effectively do so. Regional law enforcement entities throughout the country continued to exhibit an inability to distinguish human trafficking from human smuggling and lacked capacity to properly investigate and document cases, as well as to collect and organize relevant data. In addition, the government remained limited in its ability to conduct international investigations. The government did not provide or fund trafficking-specific trainings for law enforcement officials, though police and other officials received training from international organizations with governmental support during the year. Seventy-seven judges also received training on both child labor and human trafficking. The government did not report any investigations, prosecutions, or convictions of public officials allegedly complicit in human trafficking or trafficking-related offenses. For example, reports suggest local kabele or district level officials accepted bribes to change the ages on district-issued identification cards, enabling children to receive passports without parental consent; passport issuance authorities did not question the validity of such identification documents or the ages of applicants.

Protection

The government did not provide adequate assistance to trafficking victims—both those exploited internally or after migrating overseas—relying almost exclusively on international organizations and NGOs to provide services to victims without providing funding to these organizations. However, following the Saudi Arabian government’s closure of its border and massive deportation of migrant workers, officials worked quickly and collaboratively with international organizations and NGOs to repatriate and accommodate over 163,000 Ethiopian returnees from Saudi Arabia and several hundred from Yemen. The government did not report the number of victims it identified and assisted during the year. It remained without standard procedures for front-line responders to guide their identification of trafficking victims and their referral to care. During the reporting period, following the return of Ethiopians exploited overseas, the Bole International Airport Authority and immigration officials in Addis Ababa referred an unknown number of female victims to eleven local NGOs that provided care specific to trafficking victims. Typically such referrals were made only at the behest of self-identified victims of trafficking. One organization assisted 70 trafficking victims during the year—often from Saudi Arabia, Kuwait, Qatar, Yemen, and Lebanon—providing shelter, food, clothing, medical and psychological treatment without government support. The government’s reliance on NGOs to provide direct assistance to most trafficking victims, while not providing financial or in-kind support to such NGOs, resulted in unpredictable availability of adequate care; many facilities lacked sustainability as they depended on project-based funding for continued operation. Despite its reliance on NGOs to provide victims care, the government at times created challenges for these organizations as a result of its 2009 Charities and Societies Proclamation. This proclamation prohibits organizations that receive more than 10 percent of their funding from foreign sources from engaging in activities that promote—among other things—human rights, the rights of children and persons with disabilities, and justice. These restrictions had a negative impact on the ability of some NGOs to adequately provide a full range of protective services, including assistance to victims in filing cases against their traffickers with authorities and conducting family tracing.

The government operated child protection units in the 10 sub-cities of Addis Ababa and six major cities, including Dire Dawa, Adama, Sodo, Arba Minch, Debre Zeit, and Jimma; staff at the units were trained in assisting the needs of vulnerable children, including potential trafficking victims. Healthcare and other social services were generally provided to victims of trafficking by government-operated hospitals in the same manner as they were provided to other victims of abuse. The government continued to jointly operate an emergency response center in the Afar Region jointly with the IOM, at which police and local health professionals provided medical and nutritional care, temporary shelter, transport to home areas, and counseling to migrants in distress, including trafficking victims. While officials reportedly encouraged victims to assist in the investigation and prosecution of their traffickers, there were no protective mechanisms in place to support their active role in these processes. For example, Ethiopian law does not prevent the deportation of foreign victims to countries where they might face hardship or retribution. There were no reports of trafficking victims being detained, jailed, or prosecuted in 2013. The limited nature of consular services provided to Ethiopian workers abroad continued to be a weakness in government efforts. Although Employment Exchange Services Proclamation No. 632/2009 requires licensed employment agencies to place funds in escrow to provide assistance in the event a worker’s contract is broken, the Ministry of Foreign Affairs (MFA) has never used these deposits to pay for victims’ transportation back to Ethiopia. Nonetheless, in one case, a young woman in domestic servitude was pushed off the fifth story of a building by her employer in Beirut; once the victim was out of the hospital, the Ethiopian Embassy assisted in her repatriation, and upon her arrival, officials referred her to an NGO for assistance.

While officials worked to facilitate the return of stranded migrants and detainees, many of whom are believed to be trafficking victims, its focus was solely emergency assistance, with minimal direct provision of or support for longer-term protective services necessary for adequate care of trafficking victims. In April 2013, through a bilateral agreement with Yemeni officials, the Ethiopian government facilitated the return of 618 Ethiopian migrants stranded in Yemen after having failed to cross the Saudi Arabian border or been deported from Saudi Arabia. The government did not coordinate humanitarian assistance for these returnees upon their arrival in Addis Ababa. IOM coordinated subsequent returns, providing shelter at the IOM transit center in Addis Ababa, where returnees received medical care and psycho-social support while UNICEF conducted family tracing. The government did not provide financial or in-kind support to these IOM-led operations.
Beginning in November 2013, the Saudi Arabian government began massive deportation of foreign workers, who lacked proper visas or employment papers. The Ethiopian government led the repatriation and closely collaborated with IOM as part of an emergency response to the deportation of 163,000 Ethiopians from Saudi Arabia—many of whom were likely trafficking victims. Ethiopian diplomats worked to identify Ethiopian detainees stuck in 64 Saudi detention camps and various ministries met twice a week in an effort to return the migrants as rapidly as possible because of inhumane conditions within Saudi deportation camps. With a peak of 7,000 returning each day, the government partnered with IOM to provide food, emergency shelter, and medical care, and facilitate the deportees’ return to their home areas. Those requiring overnight stays in Addis Ababa were accommodated in IOM’s transit center and three transit facilities set up by the government; two of these were on government training campuses and one was rented at the government’s expense. The Disaster Risk Management and Food Security Section of the Ministry of Agriculture set up incident command centers at transit centers where representatives from all ministries addressed issues among returnees. The Ministry of Health and the Ministry of Women, Children, and Youth Affairs provided blankets, food, and the approximate equivalent of $12,000 to a local NGO that assisted 87 severely traumatized trafficking victims identified among this population—believed to be only a mere fraction of the total number of victims needing comprehensive counseling and reintegration support among these deportees. Regional governments established committees to provide returnees basic assistance and planned to support their reintegration via the establishment of cooperatives and small businesses. For example, in Addis Ababa, 3,000 returnees received psychological support and 1,743 graduated from technical skills training. While the government contributed the equivalent of approximately $2.5 million towards repatriation costs, it requested reimbursement from IOM via donors for the equivalent of approximately $27,000 worth of food.

Prevention

The government made moderate efforts to prevent human trafficking. It coordinated both regional and national awareness raising campaigns. In 2013, nationally-owned media companies aired a drama series which portrayed the dangers of being trafficked. The Women’s Development Army, a government run program, raised awareness of the dangers of sending children to urban areas alone and of the potential for abuse when illegal brokers facilitate migration. Working-level officials from federal ministries and agencies met weekly as part of the technical working group on trafficking, led by MOLSA. The inter-ministerial taskforce on trafficking met quarterly and was extensively involved in responding to the deportation of Ethiopians from Saudi Arabia.

Officials acknowledged that licensed employment agencies were involved in facilitating both legal and illegal labor migration and, as a result, enacted a temporary ban on the legal emigration of low-skilled laborers in October 2013. The ban is set to remain in place until draft amendments to the employment exchange proclamation are enacted to allow for greater oversight of private employment agencies, to mandate the placement of labor attachés in Ethiopian embassies, and to establish an independent agency to identify and train migrant workers. The government monitored the activities of labor recruitment agencies and closed an unknown number of agencies that were identified as having sent workers into dangerous conditions. Officials acknowledged that the ban may encourage illegal migration; as a result, the EFP mobilized additional resources to monitor Ethiopia’s borders. In February 2014, the EFP intercepted 101 Ethiopians led by an illegal broker at the border with Sudan. In early November 2013, the government sent a delegation of officials to Saudi Arabia to visit various camps where Ethiopians were being held. Due to the poor conditions in the camps and numerous reports of abuse, the Ethiopian government acted to remove all of their citizens swiftly. During the year, a planned government-funded, six-week, pre-departure training for migrant workers was suspended due to lack of funding. Labor migration agreements negotiated in the previous reporting period with Jordan, Kuwait, and Qatar remained in place; the government negotiated new agreements in 2013 with the Governments of Djibouti, Sudan, the UAE, and Kenya. However, these agreements did not explicitly contain provisions to protect workers—such as by outlining mandatory rest periods, including grounds for filing grievances, and prohibiting recruitment fees.

In 2013, the government established the Office of Vital Records to implement a June 2012 law requiring registration of all births nationwide; however, the lack of a uniform national identification card continued to impede implementation of the law and allowed for the continued issuance of district-level identification cards that were subject to fraud. MOLSA’s inspection unit decreased in size during the reporting period from 380 to 291 inspectors as a result of high turnover rates and limited resources. In 2013, the government’s list of Activities Prohibited for Young Workers became law. MOLSA inspectors were not trained to use punitive measures upon identifying labor violations, and expressed concern that such efforts would deter foreign investment. The government provided Ethiopian troops with anti-trafficking training prior to their deployment abroad on international peacekeeping missions, though such training was conducted by a foreign donor.