Wednesday 8 November 2017

የኦሮሚያ ቴሌቭዥን ስለ አጼ ሚኒሊክ እና ኢትዮጵያ የሰራው አነጋጋሪ ዘገባ

ኢትዮጵያዊነት


የኦሮሚያ ቴሌቭዥን ስለ አጼ ሚኒሊክ እና ኢትዮጵያ የሰራው አነጋጋሪ ዘገባ




Wednesday 27 September 2017

Stockholm, 26 September 2017 Ethiopian activist Yetnebersh Nigussie Named 2017 Right Livelihood Award Laureate


THE AWARD LIVELIHOOD RIGHT 
Press Release
Stockholm, 26 September 2017 Ethiopian activist Yetnebersh Nigussie Named 2017 Right Livelihood Award Laureate Acclaimed Ethopian activist and advocate for inclusion of people with some kind of disability, Yetnebersh Nigussie, has been announced a Laureate of the 2017 Right Livelihood Award, widely known as the ‘Alternative Nobel Prize’. 
Nigussie is recognised by the Jury “for her inspiring work promoting the rights and inclusion of people with disabilities, allowing them to realise their full potential and changing mindsets in our societies”. 
The announcement was made at the International Press Centre at the Swedish Ministry for Foreign Affairs by Ole von Uexkull, Executive Director of the Right Livelihood Award Foundation, and Maina Kiai, Jury member and former UN Special Rapporteur on the rights to freedom of peaceful assembly and of association. 
Upon receiving the news, Nigussie commented, “It is an absolute honour to receive the prestigious Right Livelihood Award. The recognition provides welcome fuel to the disability and development community’s ongoing call for inclusion and full participation of people with disabilities in all spheres of life.” 
Becoming blind at the age of five after a meningitis infection, Nigussie escaped an early marriage and was sent to the Shashemane Catholic School for the blind. The nuns running the school helped her to focus on her capabilities. Nigussie’s activism for human rights is based on her own experience of being discriminated against coming from a “developing country”, being young, a woman – and blind. 
Through her tireless efforts, she has changed perceptions on disability in her own society and internationally with the compelling message: “Focus on the person, not the disability. We have one disability, but 99 abilities to build on!” 
Currently a Senior Inclusion Advisor with the international disability and development NGO, Light for the World, Nigussie fights for the inclusion of the more than 1 billion people in the world with some kind of disability. She strives to create inclusive conditions for future generations by connecting national realities with international frameworks. 
Ole von Uexkull commented: “Yetnebersh Nigussie is a shining star of hope for all, not just for the more than 1 billion people with some kind of disability. With her personal story and her political work as an activist, she makes a strong case for positive social change, based on people’s rights and people’s abilities. With Yetnebersh Nigussie, we honour a courageous woman who shows the enormous potential of inclusive societies.” 
The 2017 cash award of SEK 3 million (EUR 315,000) is shared equally by Yetnebersh Nigussie, the human rights lawyer Colin Gonsalves (India) and the investigative journalist Khadija Ismayilova (Azerbaijan). This years’ honorary award goes to the American lawyer Robert Bilott, responsible for one of the most significant victories for environmental law and corporate accountability of this century. 
Ole von Uexkull said: “This year’s Laureates protect the rights and lives of citizens across three continents. With their courageous work for human rights, public health and good governance, they tackle some of the world’s most pressing challenges at their very core. At a time of alarming setbacks for democracy, their successes show us the way forward towards a just, peaceful and sustainable world for all.” 

Saturday 22 July 2017

ህሊና እና መንገድ

ዳንኤል ክብረት በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ መምህርና የወግ ደራሲ)
አንድ ሰው ከሚያሳድዱት ሰዎች እየሸሸ ይሮጣል፡፡ ሊያመልጥ በሚችልባቸው መንገዶች ሁሉ እየተሹሎከሎከ ተጓዘ፡፡ ሰዎቹ እንዳያዩት ሊደበቅባቸው በሚችሉ አማራጮች ሁሉ ተፈተለከ፡፡ በስተ መጨረሻ እግሩ ከአንድ ግምብ አጠገብ አደረሰው፡፡ ግንቡ እጅግ ቁመታም እና ረዥም ነበር፡፡ ተንጠላጥሎ ለማለፍም ምንም ዓይነት መወጣጫ አልነበረውም፡፡ ምናልባት የሚያስገባ ቀዳዳ ባገኝ ብሎ የግንቡን ጥግ ተከትሎ ሮጠ፡፡ ነገር ግን እርሱ ደከመው እንጂ መገቢያ ሊያገኝ አለቻለም፡፡
በመጨረሻ ተስፋ ሊቆርጥ ደረሰ፡፡ ከኋላው የሚያሳደዱት ሰዎች እንደርሱው ግንቡን ሲያዩ መጀመርያ ደነገጡ፤ በኋላ ግን እርሱን ለመያዝ አመቺ መሆኑን ዐውቀው ደስ አላቸው፡፡ ሊሄድ ይችላል በሚሏቸው በሁለቱ የግንቡ አቅጣጫዎች ተከፋፍለው ሮጡ ፡፡
ልቡ እየደከመ፣ ሃሳቡ እየዛለ፣ እንጥሉ እየወረደ፣ ሐሞቱ እየፈሰሰ፣ አንጅቱ እየራቀ፣ መቅኔው እያለቀ መጣ፡፡ «ይህንን ሁሉ መንገድ ለፍቼ ለፍቼ ሊይዙኝ ነው» ብሎም ከአንድ ዛፍ ሥር ቁጭ ብሎ አለቀሰ፡፡ ዕንባውን ጠርጎ ቀና ሲል ከግንቡ ራቅ ካለ ዛፍ ላይ የተጠጋ አንድ ሐረግ አየ፡፡ የሐረጉን ሥር በዓይኑ ሲከተለው ከግንቡ በላይ ከወጣው ዛፍ ተንጠላጥሎ ሲሳብ አየው፡፡ ጥቂት ብርታት አገኘ፡፡ ተስፋ ካለ ብርታት አለና፡፡ ሰው የሚደክመው ኅሊናው ሲደክም ነው፡፡
ጠጋ ብሎ ሐረጉን ያስጠጋውን ዛፍ ተደገፈ፡፡ ጠንካራ ነው፡፡ «ምን ላድርግ?» አለና ተጨነቀ፡፡ ያለ የሌለ ዐቅሙን አሟጠጠ እና ዛፉ ላይ ወጣ፡፡ የሐረጉንም ጫፍ ሳብ ሳብ አደረገው፡፡ ጠንካራ ነው፡፡ መልሶ መላልሶ ሳበው፤ ሐረጉ ጠንካራ ነው፡፡ ይህን ጊዜ የሰው ድምጽ ሰማ፡፡ ዝቅ ብሎ ሲያይ የሚያሳድዱት ሰዎች በአካባቢው ደርሰዋል፡፡ ደግነቱ አላዩትም፡፡
ሐረጉን በመዳፉ ጠመጠመና ወደ ኋላ ተስቦ ዛፉን በኃይል ለቀቀው፡፡ ያን ጊዜ ሐረጉ እንደ ፔንዱለም ተወርውሮ ከግንቡ በላይ አንጠለጠለው፡፡ ቋ ቋ ቋ የሚል ድምጽ ሰማና ሐረጉ ተበጠሰበት፡፡ ደግነቱ የወደቀው ግንቡ ላይ ነበር፡፡ ዘወር ሲል አሳዳጆቹ አይተውታል፡፡ የተረፈችውን ሐረግ ይዞ ወደ ምድር ወረደ፡፡
ክዚያ በኋላ የሆነውን አያውቀውም፡፡ ሮጠ ሮጠ ሮጠ እናም በቃ ሮጠ፡፡ ሲበቃው ዐረፈ፡፡ ሰውነቱ እንጂ ኅሊናው አላረፈም ነበር፡፡ እስካሁን ድረስ አንዳች ማምለጫ ለምን አላገኘሁም፡፡ ይህንን ሁሉ ስደክም ያለተገለጠልኝ መንገድ እንዴት አሁን ታየኝ? ያወጣ ያወርድ ጀመር፡፡
እናም መንፈስ እንዲህ አለው፡፡ መጀመርያኮ ትሮጥ የነበረው በኅሊናህ አይደለም በእግርህ ብቻ ነው፡፡ እግርህ መሄድ ስለቻለ እና መንገዱም ሊያስኬድህ ስለቻለ ብቻ ነው የሮጥከው፡፡ ስለቻሉ መሮጥ አና እንዲችሉ ሆኖ መሮጥ ይለያያሉ፡፡ ስለሚያስኬድ መሄድ እና እንዲያስኬድ ሆኖ መሄድ ይለያያሉ፡፡» አለው፡፡ ይኼኔ ሰውዬው ደንግጦ «እንዴት?» አለ፡፡
አንዳንድ ጊዜ አጋጣሚዎች፣ ሁኔታዎች እና መንገዶች ይመቻቹልሃል፡፡ ያንተ ሃሳብ ሳይጨመርበት እንዲሁ የሚያፈራ ፍሬ፣ የሚወጣ እንጀራ፣ የሚያተርፍ ንግድ፣ የሚያበላ ሥልጣን፣ እና የሚያስደስት ትዳር ይገጥምሃል፡፡ ይኼኔ ኅሊናህ ቦዘኔ ይሆናል፡፡ መሄድህን እንጂ መድረሻህን አታውቀውም፡፡
እንዲህ የሆኑ ሰዎች እንዳንተ የተዘጋ የመሰለ ግንብ ሲገጥማቸው ይደነግጣሉ፡፡ ቦዘኔ የነበረ ኅሊናቸውን ቀስቅሰው ማሠራት ይከብዳቸዋል፡፡ ቦዘኔ ኅሊናን ከመቀስቀስ ደግሞ የሞተ የመኪና ባትሪ መቀስቀስ ይሻላል፡፡
አጋጣሚኮ መነሻ እንጂ መድረሻ መሆን የለበትም፡፡ የበረደን የመኪና ሞተር በባትሪ እንደ ሚያስነሡት የተኛን ኅሊና በአጋጣሚዎች ሊቀሰቅሱት ይቻላል፡፡ መኪናን በባትሪ ኃይል አይነዱትም፡፡ ሕይወትንም በአጋጣሚ አይመሯትም፡፡
አንድ ነጋዴኮ በአጋጣሚ ጥሩ ቦታ ላይ ስላለ፣ ዕድለኛም ስለሆነ፣ ብቸኛም ስለሆነ፣ ጊዜውም ስለረዳው፣ ሊበለጽግ ይችላል፡፡ እነዚህ ሁሉ ግን የኅሊናን ርዳታ ሳይፈልጉ እንደ አንተ እግር የሚኳትኑ ናቸው፡፡ አንተኮ ለጊዜው አምልጠሃል፤ ሸሽተሃል፤ መፍትሔ አግኝተሃል፡፡ ነገር ግን ኅሊናን የሚጠይቅ ጊዜ ላይ ስትደርስ ነበር የተሸነፍከው፡፡ ያም ነጋዴ ኅሊናን የሚጠይቅ አንድ ቀን ያጋጥመዋል፡፡ ዕድል ተበላሽቶ፣ ዘመን ተቀይሮ፣ ባለ ሥልጣን ወርዶ፣ ኑሮ ተለውጦ፣ ቦታውንም ተቀምቶ፣ ተወዳዳሪም በዝቶ ያ እንደ ልቡ የሚሮጥበት መንገድ የተዘጋ ሊመስለው ይችላል፡፡
ታድያ ያን ጊዜ ተኝቶ የኖረን ቦዘኔ ኅሊና መቀስቀስ ከባድ ነው፡፡
በጣልያን ጊዜ ከጣልያን ጋር አብረው ሕዝባቸውን እየወጉ በዘመኑ የሚጠቀሙ ሰዎች ነበሩ፡፡ ዘመኑ የሰጣቸውን ከመብላት፣ ከመጠጣት፣ ከመሾም፣ ከማጋበስ፣ ከመላላክ፣ በቀር ኅሊናቸውን ያልተጠቀሙ፡፡ ቦዘኔ ኅሊና የነበራቸው ሰዎች፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ አጋጣሚውን ዕውቀት ለመቅሰም፣ ሥልጣኔን ለመማር፣ ሞያ ለመልመድ የተጠቀሙበት ባለ ኅሊናዎችም ነበሩ፡፡ በአንድ በኩል ከጣልያን የሚያስቀሩትን እያስቀሩ በሌላ በኩል የውስጥ አርበኞች ሆነው የሠሩ ንቁ ኅሊና ያላቸው ሰዎች ነበሩ፡፡
ታድያ ሕዝቡ በእነዚያ ቦዘኔ ኅሊና ባላቸው ሰዎች በማዘኑ የተነሣ
አርኩም ይሄድና
ሶልዲውም ያልቅና
ያስተዛዝበናል ይሄ ቀን ያልፍና
ብሎ ገጠመ ይባላል፡፡ ብዙዎቹ አስበውበት አልነበረም የኖሩት፤ እንዴው ዘመን የወደደውን፣ ጊዜ የወለደውን ሲያደርጉ እንጂ፡፡ ሆዴ ይሙላ ደረቴ ይቅላ ብለው እንጂ፡፡ ታድያ በኋላ ተቸገሩ፡፡ አርኩም ሄደና ሶልዲውም አለቀና ተቸገሩ፡፡ የቦዘነ ኅሊናቸውን ተነሥ ቢሉት እምቢ አላቸው፡፡ ትርፍራፊ እና ልቅምቃሚ ለምዶ፣ ችሮታ እና ስጦታ ለምዶ አሁን ምን ይዋጠው፡፡
አየህ ምግብ ቀረበ ተብሎ ያለ አሳብ አይበላም፣ አልጋ ተመቸ ተብሎ ያለ አሳብ አይተኛም፡፡ ጨዋታ ደራ ተብሎ ያለ ልክ አይወራም፤ ገንዘብ አለ ተብሎ ያለ መጠን አይወጣም፤ እግር አለ ተብሎ ያለ ምዕራፍ አይኬድም፡፡ ይህ ኅሊናን ማቦዘን ነው፡፡
ለመሆኑ ለምን ነበር ያ ሐረግ የታየህ?
አማራጭ አልነበረህም፡፡ አሁን እግር እንደወሰደ የሚኬድበት መንገድ የለም፡፡ ያለው ግንቡ ብቻ ነው፡፡ የግድ ኅሊናህ መሥራት ነበረበት፡፡ አሁን አጋጣሚዎች አያጋጥሙህም አጋጣሚ ትፈጥራለህ እንጂ፤ መንገድህ አልቋል መንገድ ታበጃለህ እንጂ፡፡ ስለዚህ ኅሊናህ በውጥረት መሥራት ጀመረ፡፡ ያን ጊዜ ሐረጉን አየኸው፡፡
ማየት አቅቶህ እንጂ እዚህ ድረስ ሳትደክም ልታመልጥባቸው የምትችል አያሌ መንገዶች ነበሩህ፡፡ አንተ ግን ኅሊናህን ስላቦዘንከው ልታያቸው አልቻልክም፡፡ እንዲሁ እግርህ እንደሄደልህ፣ መንገድ እንደወሰደህ፣ አገር እንደ ቀናህ ነበር የምትሮጠው፡፡ ታድያ እንዴት ታየው?
ዝግ ኅሊና እንጂ ዝግ መንገድ የለም፡፡
መንገድ የሚከፈተው ኅሊናህ ውስጥ ነው፡፡ አስቀድመው በኅሊና መንገድ ወደ ጨረቃ የሄዱ ሰዎች በኋላ በመንኮራኩር መንገድ ለመሄድ አልቸገራቸውም፡፡ የኅሊናቸው መንገድ ዝግ የሆነባቸው ግን ይኼው አሁንም «ጨረቃ ድንቡል ቦቃ ዐጤ ቤት ገባች ዐውቃ» እያሉ በመዝፈን ላይ ናቸው፡፡
ማጂላን ዓለምን ከመዞሩ በፊት ኅሊናው ዓለምን ዞሮ ነበር፤ ቫስኮ ዳጋማ ሕንድ ከመድረሱ በፊት ኅሊናው ደርሶ ነበር፡፡ ዋናው ኅሊና ነው፡፡ አስቀድሞ ኅሊናቸው የጸደቀ ሰዎች እኮ ናቸው በኋላም አካላቸው የሚጸድቀው፡፡
መኖር ማለት ማግኘት አይደለም፤ መኖር ማለት መትረፍረፍ አይደለም፤ መክበር እና መንፈላሰስ አይደለም፡፡ መኖር ማለት ማሰብ ነው፡፡ በሥጋ ሳይሆን በኅሊናህ ኑር፡፡ በኅሊናህ ከኖርክ የተዘጋ መንገድ የለም፡፡ ቢኖርም ትከፍተዋለህ፡፡
አንድ ታሪክ ልንገርህ፡
አንድ ፈላስፋ ነበር አሉ፡፡ አንድ ቀን መንገድ ሲሄድ መሸበትና ከአንድ ዛፍ ሥር ዐረፍ አለ፡፡ ጨለማው እንደ ግብጽ ጨለማ የተጠቀጠቀ ነበር፡፡ ፈላስፋው ምናልባት አንዳች ነገር በዚህ ጨለማ ውስጥ ብመለከት አለና ዓይኑን ፍጥጥ አድርጎ ማየት ጀመረ፡፡ መጀመሪያ አካባቢ ዓይኑን ደከመው፡፡ እየጨፈነ እና እየገለጠ ማየት ቀጠለ፡፡ ትንሽ ቆይቶ የሆነ የብርሃን ጭላንጭል ታየው፡፡ እየቆየ ሲሄድ አካባቢውን በደምሳሳው ማየት ቻለ፡፡ ትንሽ ቆይቶ ደግሞ ከፊት ለፊቱ ያለው የበቆሎ እርሻ መሆኑን ለየ፡፡ በመጨረሻም በእርሱ እና በበቆሎ እርሻው መካከል የጥበቃ ማማ ታየው፡፡
ወዲያው አፈፍ አለና ተነሣ፡፡ ወደ ማማው ሄዶ በዚያ አደረ፡፡ በአውሬ ከመበላትም ዳነ፡፡ ይህ ፈላስፋ ታድያ ምን አለ መሰለህ «ማየት ለሚችል ሰው በጨለማ ውስጥ ብርሃን አለ፡፡ ጨለማን ጨለማ ያደረገው የፀሐይ መጥፋት ሳይሆን የኛ አለማየት ነው» አለ፡፡
እኔስ የኅሊና እንጂ የመንገድ ዝግ የለውም ያልኩህ ይህንኑ አይደል?
ይህንን ነግሮት መንፈሱ ከእርሱ ተለየ፡፡ መንገደኛውም የመንፈሱን ትሩፋት ተቀብሎ ሄደ፡፡ ይህንን ከወሬ ወሬ የሰማ አንድ ሰውም እነሆ በብሎጉ ላይ ጻፈው፡፡

Tuesday 9 May 2017

Singer Teddy Afro's New Album Holds Fast to His Vision of a Diverse, Yet United Ethiopia




























Ethiopian singer Teddy Afro, who delivered opening remarks at a U.S. Embassy-sponsored workshop for students on the occasion of World Environment Day 2015. Photo by U.S. Embassy Addis Ababa; CC BY-ND 2.0.
Ethiopian singer Tewodros Kassahun’s most anticipated and highly promoted studio album was released to great fanfare at the beginning of May 2017.

More popularly known as Teddy Afro, his latest album — his fifth — comprises 15 songs of tribute and love that touch on issues of solidarity, reconciliation and the hope of living collectively in a diverse country. The album also includes a song with lyrics in a coded language, which is being interpreted by some as a rebuke to his detractors.

Ever since he caught the public's attention with his debut album in early 2001, Teddy Afro has been a household name in Ethiopia. He is a melodic singer and prolific songwriter. “Ethiopia”, a single that appeared on his new album, racked up millions of views on YouTube as soon as it was released. His album attracted sales of up to 6 million Ethiopian Birr — a feat that no other Ethiopian singer has ever managed to accomplish — which is telling commentary on his popularity.



The recurring theme in Afro's albums, is the need to nurture countrywide harmony, unity, and love which transcend ethnic and religious boundaries in his beloved Ethiopia.

Expanding upon this foundation, this latest album solidifies this message, both in thematic content and lyrics. While the album is mainly an Amharic language pop music offering, some segments of lyrics are inserted into his Amharic songs from other Ethiopian languages, such as Afan Oromo, Tigeregna, and Sidama, which all reflect the singer’s philosophy and interests.

He blends his version of reggae with Ethiopian beats, styles, and instruments. His deployment of the sound of mesenqo, a single-stringed Ethiopian bowed lute, which he mixes delicately with acoustic guitar, bass guitar and drums — while he sings in Amharic and Afan Oromo on one of the tracks — is a great example.

The response to Afro's album has been mixed. Teddy’s fans and detractors either apotheosize or admonish him based on his fame, his lyrical perspective — even his album's cover art.

His enthusiasts adore him for his genius, while his detractors accuse him of simplifying the complex history of Ethiopia.

Music meets politics

The near-fanatical appreciation for — and opposition to — Afro’s latest album is an indication that, in Ethiopia, music criticism usually melds together with political ideology.

Since the release of the album’s single, “Ethiopia”, three weeks ago, much of the debate on social media has been about the politics of Afro's songs. He received an unprecedented amount of criticism for being simplistic — penning lyrics that misrepresent the history of Ethiopia, the poetic quality of which, some believe, mixes cliché and nonsense.

As political concerns take priority over the quality of the music, the artistic aspects of Afro’s work are receiving less attention. However, there are some critics who falsely accuse him of recycling melody lines from his earlier albums, or even plagiarizing other people’s songs.

Powerful, yet vulnerable

As much as Afro is a prominent and influential artist, he is also a vulnerable one — producing socio-politically conscious songs while operating in a politically hostile environment. Ethiopian authorities have been known to censor political expressions, whether journalistic or cultural.

Afro was once denied playing a gig in the country's capital, after authorities refused to issue a permit for the concert. He was also prevented from leaving the country for a concert abroad. In 2014, some individuals campaigned against him to strong-arm a beer company to cancel its sponsorship of Teddy’s national music tour over an alleged “politically insensitive” comment in an unpublished weekly magazine.

In 2005, when he released his second album, Afro was aligned with opposition politics because five of his songs were overtly political. One signature song in particular, “Jah Yastserial” can be read as a call for reconciliation among Ethiopian political opponents, a praise for Emperor Haile Selassie or, most plausibly, a critique of the Ethiopian government for failing to live up to its promise. Many consider this song as a popular anthem of anti-government protesters, as it resonates well with the mood of the post-election political turmoil of the 2005 parliamentary elections.

In 2008, Afro was arrested, charged with a hit and run, taken to jail and held there for almost two years. He denied he committed the alleged crime, and most of his fans claim the allegations are false and politically motivated.

While Afro does not fit the rebellious image of an overtly political singer, he forcefully asserts a collective version of Ethiopian history, culture, and identity, without bowing to pressure to adopt a political posture.

A vision of Ethiopia

In Ethiopian history, the dominant ideology was a national identity based on a shared, yet hybrid cultural and ethnic solidarity, with a modernizing project based on claims of Ethiopia’s 3000 years of “collective memory”. However, this project came to an abrupt stop in 1991, when two decades of civil war ended. The current regime defined “communities” based on their ethnic identity, and reorganized the Ethiopian state structure exclusively based on this — a deliberately administered, radical break with Ethiopia’s past.

Many blame the current regime for the gradual erosion of the shared Ethiopian identity. In what appears to be a response to the government’s over-emphasis on ethnic identity, Afro's songs pay tribute to early Ethiopian civilization, history, and culture. He praises national figures of the past and considers them as enlighteners. In his latest album, he honored Tewodros II, a 19th century Ethiopian emperor who fought the British. In his fourth album, he did the same for Emperor Menelik II, who defeated the Italians in 1896 at the Battle of Adwa.

His assertion of a shared Ethiopian identity and national pride in an era of ethnic federalism, in which the regime has denied the existence of collective Ethiopian identity, is a potential threat.

For government supporters and ethnonationalists alike, Afro is a familiar villain. His tributes to past Ethiopian leaders and his devotion to “love and unity” represent an old Ethiopia, a defeated ideology.

Nevertheless, he continues to be a magnetic figure for younger generations and exerts a vast influence among his compatriots. Despite claims that Afro’s songs represent a defeated ideology, his albums generate sales on a record scale — and his fan base is passionate enough to overwhelm the Ethiopian internet and send the message that they are taking a relaxing break from repression.

Friday 21 April 2017

እየራበው ካሴት የሚገዛ ህዝብ



Megabi Hadis Eshetu Alemayehu

ፀሎታችን እንዲሰማ እንዴት ብለን እንፀልይ?






Wednesday 19 April 2017

ሰከን በሉ



እንደ ንዋይ ደበበ እና ቅንድቦ ሆድ አደር ሳይሆን ሰርቶ አደር ነዉ እንደ ጃኪ ጎሲ ሃሺሽ ቤት የለውም  የሚዘፈነውን የሚናገረውን የሚኖር ፈርሃ እግዚአብሄር ያለው ትሁት የጥበብ ሰው  በመያው መስዋትነት የከፈል ለኢትዮጵየ ኪነ ጥበብን ያአሳደገ ለሌሎች የሙያ አጋሮቹ አርዓያ የሆነ በራስ መተማመን እንዲኖራችው ያደረገ በሃገሩ ላይ ቢታስር ቢገፋ እንዳይሰራ ሲታገድ `` ይዤ አላነሳም እጄን ከቀሚሷ፣
እናት እኮ ናት ተስፋ አልቆርጥ በሷ፤
ቢጎል እንጀራው ከመሶቡ ላይ
እናት በሌላ ይቀየራል ወይ…
አየናችሁ እኮ ድሃ እናት ሃገራችሁን ባለው የቀየራችሁ የድል አጥቢያ አርበኞች  ልብ ያለው ልብ ይበል ጆሮው ያልው ያድምጥ
ቢጎል እንጀራው ከመሶቡ ላይ
እናት በሌላ ይቀየራል ወይ…
አንድ ዝግጅት ስቀርብ ስዓቱ፣ የበዓል ቀን ነው ውይስ አዘቦት የዝግጅቱ ተከታታዮች
ርዮት ሙያዊ ትችት ሌላ ዘለፋ ሌላ በተለይ ቴዲ ስትናገር ስነ ምግባር የለህም ሰዎችን ቃለ መጠይቅ ስታደርግ ለምሳሌ ድ ር ፍቅሬ ቶሎሳን ሠራዊት ፍቅሬን ሌሎችንም ከድምፅ አወጣጥህ ጀምሮ ሰከን በል ከበላይ አካል ተልክህ ነው ወይስ ብላቴናውን በመተችት ዝና ፍለጋ ባልፍም ኖሬ ስለ እናት ምድሬ እሷ ናት ክብሬ ኽረ እኔስ ሃገሬ

ከፈለገ ጊዮን

የቴዎድሮስ ካሳሁን  (ቴዲ አፍሮ) ጥፋቱ ምንድን ነው?

by 

መስፍን ወልደ-ማርያም
ሰኔ 2006 ዓ.ም
ቴዎድሮስ ካሣሁንን በአካል አላውቀውም፤  በዘፈንና በጭፈራ በእውነት ተደሳች መሆን ካቃተኝ ቆይቷል፤ ከ ኅዳር 1967 ጀምሮ ነው የቆረቆረኝ፤ ይህ ሰው እንደሰውና እንደ ኢትዮጲያዊ በየጊዜው የሚደርስበትን ወደ ግፍ የሚጠጋ በደል ስመለከት ያው የለመድነው ምቀኝነት ነው እያልሁ ሳልፈው ቆየሁ፤ ግን በደሉ አላቆም አለ፤ ማንም ሊደርስለት አለመቻሉ ይበልጥ ያሳዝናል፣ በእሱ ላይ ተከታታይ  የደረሰበት በደል የሕግ ያለህ የሚያሰኝ ነው፤ በቴዎድሮስ ካሣሁን ላይ በተቀነባበረ መንገድ የሚፈፀመው ማሰቃየት ማንንም ሰው የሚያሳስብ ነው፤ ምክንያቱ ምንድን ነው? በግልጽ የታወቀ ነገር የለም።
በቴዎድሮስ ላይ ከባድ ተንኮል ሲፈጸምበት የሰማሁት በመጀመሪያ ዛሬ በስደት ላይ ባለው « አዲስ ነገር» የሚባል ጋዜጣ ላይ ነበር፤ ጋዜጣው ቴዎድሮስ በሙያው ያገኘውን መልካም ስም በሰፊው ጥላሸት ቀብቶት ነበር፤ በጣም ሰፊ የሆነ ሀተታ በቴዎድሮስ ዘፈኖች ላይ በማቅረባቸው ምን ያህል አንገብጋቢ የአገር ጉዳይ አግኝተውበት ይሆን ብዬ አነበብሁት፣ ምንም ለአገር  የሚጠቅም ጉዳይ አላገኘሁበትም፤ በዘፈኖቹ ላይ በተደረገው ሂስም ከጋዜጠኞቹ መሀከል የሙዚቃ ሙያ ባለቤት እንዳለ ብጠይቅም ጋዜጣው ባለሙያ እንደሌለውና ስሙ እንዲጠቀስ ያልፈለገ ባለሙያ ማማከራቸውን ነገሩኝ፣  ስሙ  እንዲጠቀስ የማይፈልግ ባለሙያ፣ ባለሙያ አይባልም፣ እንኳን በሙያው በራሱም አይተማመንም ማለት ነው፤ በዚህ በራሱ በማይተማመን ሰው ምስክርነት ላይ በተመሰረተ ረጅም ነቀፌታ ቴዎድሮስን ደበደቡት፤
ሁለተኛው የቴዎድሮስ ጣጣ በመኪና ሰው ገጭቷል ተብሎ መከሰሱ ነው፤ በሌሊት፣ በጨለማ ነው፤ ቴዎድሮስ እንደሚለው  «እኔ ወደአገሬ የገባሁት ሰውዬው ሞተ በተባለበት ቀን ማግስት እንደሆነ ቪዛዬ ያረጋግጣል፣»  (ነጋድራስ መስከረም 30/2001 ዓ.ም. ) በኋላም ከዳግማዊ ምኒልክ ሆስፒታል የተገኘው መረጃ ይህንኑ የሚያረጋግጥ እንደነበረ ተነግሮአል፤  በዚሁ በነጋድራስ ጋዜጣ ላይ የሚከተሉት መረጃዎች ተጠቅሰዋል ፦
  1. ቴዎድሮስ ከውጭ የተመለሰው በ22/2/1999 ዓ.ም መሆኑ
  2. ሰውዬው በ 22/1/1999 ሞቶ አስከሬኑ በ22/2/1999 ዓ.ም መመርመሩን የጽሑፍ ማስረጃ፣
  3. ዓቃቤ ሕግና ፖሊስ በሆስፒታሉ የተገለጸው የምርመራ ቀን እንዲለወጥ መጠየቃቸው፣
  4. ከአሥራ ሦስት ቀኖች በኋላ በተደረገ ምርመራ መኪናው ላይ ምንም ደም አለመገኘቱን፣
ይህ ሁሉ ሆኖ በቴዎድሮስ ላይ ተፈርዶበት ወህኒ ወርዶ ጊዜውን ጨርሶ ከወጣ ቆይቶአል።
ከዚያ ወዲህ ደግሞ በተቀነባበረ ሁኔታ ቴዎድሮስ ካሣሁን በዘፈኑ ያገኘውን ዝና ለማጉደፍና በሥራውም የሚያገኘውን ጥቅም ለመቀነስ ተግተው የሚሠሩ ሰዎች መኖራቸውን የሚያመለክቱ ነገሮች አሉ፣ በመጀመሪያ ቴዎድሮስ በኢትዮጵያና በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የፈጸመው በደል ከአለ ግልጽ ሆኖ ቢወጣና ሁላችንም ብናውቀው ጥሩ ነው፤ አለዚያ ግን እየተደራጁ አንድ ግለሰብን ለማጥቃት የሚደረገው እርምጃ የሚወገዝና ልንቃወመው የሚገባ ጉዳይ ነው፣  አንድን ሰው በእምነቱ፣ በአስተያየቱ፣ ወይም ስኬታማነቱን በመመቅኘት ለመጉዳት ዓለም -አቀፋዊ ሴራ ማካሄድ ክፋት ነው፤ ይህንን ክፋት አምጠው የወለዱትና ለማሳደግ የሚሞክሩት ሰዎች፤ የማሰብ ችግር ያለባቸውና ክፋታቸው ተመልሶ እነሱኑ የሚያጠቃ መሆኑን የመገንዘብ ችሎታ  እንኳን የሌላቸው ናቸው።
ሦስተኛው የቴዎድሮስ ስቃይ የበደሌ ቢራ ፋብሪካ በቴዎድሮስ ዘፈን ለመጠቀም ሲፈልግ፣ የጨለማ ሰዎች ተሰብስበው በቴዎድሮስ ዘፈን የታጀበውን የበደሌ ቢራ እንደማይጠጡ በመዛታቸው ኩባንያው ከቴዎድሮስ ጋር የነበረውን ውል መሰረዙ ነው፤  እንደተገነዘብሁት ቴዎድሮስ ትንሽ በቁንጫ ተሰቃየ እንጂ ክፍያው አልቀረበትም፣ ነገር ግን ቴዎድሮስን አንደሰው፣ እንደኢትዮጵያዊ፣ እንደዘፋኝ የሚያውቁት ሰዎች የሉም፤ ወይም በጨለማዎቹ ሰዎች ተሸንፈዋል፤ ወይም በፍርሃት ቆፈን ደንዝዘዋል! የጨለማ ሰዎቹ ቴዎድሮስ ካለበት አንጠጣውም የተባለው ቢራ ለቴዎድሮስ ወዳጆች እንዴት ጣፈጣቸው?
አራተኛው የቴዎድሮስ ስቃይ የመጣው ሦስተኛውን ጥቃት ለመቋቋምና ለማረም ምንም ዓይነት የማረሚያ እርምጃ ስላልተወሰደ ነው፤ የበደሌ ቢራ ኩባንያ እንዳደረገው ሁሉ የኮካኮላ ኩባንያም ቴዎድሮስ ካሣሁንን ለአሻሻጭነት መረጠ፤  የጨለማዎቹም  ሰዎች እንደገና ተነሡ፤  ቴዎድሮስን ካልሻራችሁ ኮካ ኮላ አንጠጣም  ብለው የቴዎድሮስ ውል እንዲፈርስ አደረጉ፤  አሁንም ቁንጫው ትንሽ ምቾቱን ከመቀነሱ በስተቀር ቴዎድሮስ ገንዘቡን አላጣም፤ አሁንም የቴዎድሮስ ወዳጆች ነን የሚሉ ኮካ ኮላ እየጣፈጣቸው ይጠጣሉ፤ ትንሽ ቆራጦች የጨለማ ሰዎች  በአደባባይ ምላሱን እየሳለ እልል ከሚለውና ከሚጨፍረው ነፍሰ-ቢስ ስብስብ ምን ያህል እንደሚበልጡና ውጤታማ እንደሚሆኑ ያሳያል።
የቴዎድሮስ ካሣሁን ጉዳይ የአንድ ግለሰብ የሰብዓዊ መብት ጉዳይ ነው፤ የጨለማ ሰዎቹ ግን ወደግለሰብነት ደረጃ ገና ያልደረሱ ናቸው፤ ስለዚህም ቴዎድሮስን እንደሰው እንዳያዩት እዚያ ገና አልደረሱም፤ እንደኢትዮጲያዊ እንዳያዩት መናፍቃን ናቸው፤ እንደዘፋኝ እንዳያዩት ጆሮአቸው አይሰማም።
በአዲስ ነገር ተጀምሮ እስካሁን አልበርድ ያለው ቴዎድሮስን ነጥሎ የማጥቃት ዘመቻ ምክንያቱ ምንድን ነው? በጥሞና ሊታይና ሊመረመር የሚገባው በአዲስ ነገር ጋዜጣና በጨለማዎቹ ሰዎች መሀከል ያለ የሚመስለው ድርጅታዊ ግንኙነት ነው፤  የአንድ ግለሰብን ሰብዓዊ መብቶች እየደጋገሙ በመርገጥ አጋጣሚ እየፈለጉ ማጥቃት የሚጎዳው ተረጋጩን ብቻ ሳይሆን ረጋጮቹንና የጋን ወንድሞችንም ነው፤ አንድ ቀን ግፍ ወደተነሣበት ይመለሳል።

Sunday 12 March 2017

የአዲስ አበባው ቆሼ ተራ ዕልቂት - የዓለምነህ ዋሴ ዘገባ


በአዲስ አበባ ከተማ ቆሼ ተብለው በሚጠራው ቦታ በደረስው አደጋ ለሞቱት ወገኖቻችን ነፍስ ይማርልን