Sunday 15 December 2019

ጌታ ነግሮኛል በሚል የ3 ሚሊየን ብር ቤቷን በ370 ሺህ ብር እንድትሸጥ አልያ ልጅሽ ትሞታለች በሚል የተጭበረበረችው አሳዛኝ ወጣት


[በእኔ የደረሰ አይድረስባችሁ] እስራኤል ዳንሳ በ ወ/ሮ እንግዳ የሺጥላ ላይ ያደረሰው አስነዋሪ ግፍ ተጋለጠ ክፍል 2


የ 3 ሚሊየን ብር ሆቴል በፓስተሩ የተዘረፈችው ወጣት ወ/ሮ እንግዳ የሺጥላ ትናገራለች ክፍል 1


ባለ ትዳርዋን የደፈራት ፓስተር ቄስ ግርማ ዘውዴ


በፓስተር ይዲዲያ ጳውሎስ ትንቢት ምክኒያት ህይወቱ ያለፈው አሳዛኝ ወጣት ቄስ ግርማ ዘውዴ ይናገራሉ


የማፍያ ፓስተሮች ጉድ] የሞተ አስነሳልሁ ብሎ ጉድ የሆነው ኢትዮጵያዊ ፓስተር እና ሌሎች ገመናዎች በቄስ ግርማ ዘውዴ


Wednesday 11 December 2019

Ethiopians heroes



Nobel Peace Prize Winner 2019






Derartu Tulu, Selomon Barega IAAF Best of 2019



2019 CNN Hero Of The Year Freweini Mebrahtu






Martha Gebeyehu of Ethiopia receives OU’s International Water Prize




Ethiopian Dr Zebib Yenus Wins African Research Award



Sosina Tewabe Wegayehu—an Extraordinary Leader!




Mr. Tewolde GebreMariam, CEO of Ethiopian Airlines wins Airline Executive of the Year organized annually by CAPA Global Aviation.

Tuesday 10 December 2019

For you to have a peaceful night, your neighbor shall have a peaceful night as well


Your Majesties, Your Royal Highnesses,
Distinguished members of the Norwegian Nobel Committee,
Fellow Ethiopians, Fellow Africans, Citizens of the World
Ladies and Gentlemen,
I am honored to be here with you, and deeply grateful to the Norwegian Nobel Committee for recognizing and encouraging my contribution to a peaceful resolution of the border dispute between Ethiopia and Eritrea.
I accept this award on behalf of Ethiopians and Eritreans, especially those who made the ultimate sacrifice in the cause of peace.
Likewise, I accept this award on behalf of my partner, and comrade-in-peace, President Isaias Afeworki, whose goodwill, trust, and commitment were vital in ending the two-decade deadlock between our countries.
I also accept this award on behalf of Africans and citizens of the world for whom the dream of peace has often turned into a nightmare of war.
Today, I stand here in front of you talking about peace because of fate.
I crawled my way to peace through the dusty trenches of war years ago.
I was a young soldier when war broke out between Ethiopia and Eritrea.
I witnessed firsthand the ugliness of war in frontline battles.
There are those who have never seen war but glorify and romanticize it.

They have not seen the fear,
They have not seen the fatigue,
They have not seen the destruction or heartbreak,
Nor have they felt the mournful emptiness of war after the carnage.
War is the epitome of hell for all involved. I know because I have been there and back.
I have seen brothers slaughtering brothers on the battlefield.
I have seen older men, women, and children trembling in terror under the deadly shower of bullets and artillery shells.
You see, I was not only a combatant in war.
I was also a witness to its cruelty and what it can do to people.
War makes for bitter men. Heartless and savage men.
Twenty years ago, I was a radio operator attached to an Ethiopian army unit in the border town of Badme.
The town was the flashpoint of the war between the two countries.
I briefly left the foxhole in the hopes of getting a good antenna reception.
It took only but a few minutes. Yet, upon my return, I was horrified to discover that my entire unit had been wiped out in an artillery attack.
I still remember my young comrades-in-arms who died on that ill-fated day.
I think of their families too.
During the war between Ethiopia and Eritrea, an estimated one hundred thousand soldiers and civilians lost their lives.
The aftermath of the war also left untold numbers of families broken. It also permanently shattered communities on both sides.
Massive destruction of infrastructure further amplified the post-war economic burden.
Socially, the war resulted in mass displacements, loss of livelihoods, deportation and denationalization of citizens.
Following the end of active armed conflict in June 2000, Ethiopia and Eritrea remained deadlocked in a stalemate of no-war, no-peace for two decades.
During this period, family units were split over borders, unable to see or talk to each other for years to come.
Tens of thousands of troops remained stationed along both sides of the border. They remained on edge, as did the rest of the country and region.
All were worried that any small border clash would flare into a full-blown war once again.
As it was, the war and the stalemate that followed were a threat for regional peace, with fears that a resumption of active combat between Ethiopia and Eritrea would destabilize the entire Horn region.
And so, when I became Prime Minister about 18 months ago, I felt in my heart that ending the uncertainty was necessary.
I believed peace between Ethiopia and Eritrea was within reach.
I was convinced that the imaginary wall separating our two countries for much too long needed to be torn down.
And in its place, a bridge of friendship, collaboration and goodwill has to be built to last for ages.
That is how I approached the task of building a peace bridge with my partner President Isaias Afeworki.
We were both ready to allow peace to flourish and shine through.
We resolved to turn our “swords into plowshares and our spears into pruning hooks” for the progress and prosperity of our people.
We understood our nations are not the enemies. Instead, we were victims of the common enemy called poverty.
We recognized that while our two nations were stuck on old grievances, the world was shifting rapidly and leaving us behind.
We agreed we must work cooperatively for the prosperity of our people and our region.
Excellencies, Ladies and Gentlemen,
Today, we are reaping our peace dividends.
Families separated for over two decades are now united.
Diplomatic relations are fully restored.
Air and telecommunication services have been reestablished.
And our focus has now shifted to developing joint infrastructure projects that will be a critical lever in our economic ambitions.
Our commitment to peace between our two countries is iron-clad.
One may wonder, how it is that a conflict extending over twenty years, can come to an amicable resolution.
Allow me to share with you a little about the beliefs that guide my actions for peace.
I believe that peace is an affair of the heart. Peace is a labor of love.
Sustaining peace is hard work.
Yet, we must cherish and nurture it.
It takes a few to make war, but it takes a village and a nation to build peace.
For me, nurturing peace is like planting and growing trees.
Just like trees need water and good soil to grow, peace requires unwavering commitment, infinite patience, and goodwill to cultivate and harvest its dividends.
Peace requires good faith to blossom into prosperity, security, and opportunity.
In the same manner that trees absorb carbon dioxide to give us life and oxygen, peace has the capacity to absorb the suspicion and doubt that may cloud our relationships.
In return, it gives back hope for the future, confidence in ourselves, and faith in humanity.
This humanity I speak of, is within all of us.
We can cultivate and share it with others if we choose to remove our masks of pride and arrogance.
When our love for humanity outgrows our appreciation of human vanity then the world will know peace.
Ultimately, peace requires an enduring vision. And my vision of peace is rooted in the philosophy of Medemer.
Medemer, an Amharic word, signifies synergy, convergence, and teamwork for a common destiny.
Medemer is a homegrown idea that is reflected in our political, social, and economic life.
I like to think of “Medemer” as a social compact for Ethiopians to build a just, egalitarian, democratic, and humane society by pulling together our resources for our collective survival and prosperity.
In practice, Medemer is about using the best of our past to build a new society and a new civic culture that thrives on tolerance, understanding, and civility.
At its core, Medemer is a covenant of peace that seeks unity in our common humanity.
It pursues peace by practicing the values of love, forgiveness, reconciliation, and inclusion.
Excellencies, Ladies and Gentlemen,
I come from a small town called Beshasha, located in the Oromia region of Western Ethiopia.
It is in Beshasha that the seeds of Medemer began to sprout.
Growing up, my parents instilled in me and my siblings, an abiding faith in humanity.
Medemer resonates with the proverb, “I am my brother’s keeper. I am my sister’s keeper.”
In my little town, we had no running water, electricity, or paved roads. But we had a lot of love to light up our lives.
We were each other’s keepers.
Faith, humility, integrity, patience, gratitude, tenacity, and cooperation coursed like a mighty stream.
And we traveled together on three country roads called love, forgiveness, and reconciliation.
In the Medemer idea, there is no “Us and Them.”
There is only “US” for “We” are all bound by a shared destiny of love, forgiveness, and reconciliation.
For the people in the “Land of Origins” and “The 13 Months of Sunshine,” Medemer has always been second nature.
Ethiopians maintained peaceful coexistence between the followers of the two great religions because we always came together in faith and worship.
We, Ethiopians, remained independent for thousands of years because we came together to defend our homeland.
The beauty of our Ethiopia is its extraordinary diversity.
The inclusiveness of Medemer ensures no one is left behind in our big extended family.
It has also been said, “No man is an island.”
Just the same, no nation is an island. Ethiopia’s Medemer-inspired foreign policy pursues peace through multilateral cooperation and good neighborliness.
We have an old saying:
“በሰላም እንድታድር ጎረቤትህ ሰላም ይደር”
“yoo ollaan nagayaan bule, nagaan bulanni.”
It is a saying shared in many African languages, which means, “For you to have a peaceful night, your neighbor shall have a peaceful night as well.”
The essence of this proverb guides the strengthening of relations in the region. We now strive to live with our neighbors in peace and harmony.
The Horn of Africa today is a region of strategic significance.
The global military superpowers are expanding their military presence in the area. Terrorist and extremist groups also seek to establish a foothold.
We do not want the Horn to be a battleground for superpowers nor a hideout for the merchants of terror and brokers of despair and misery.
We want the Horn of Africa to become a treasury of peace and progress.
Indeed, we want the Horn of Africa to become the Horn of Plenty for the rest of the continent.
Excellencies, Ladies and Gentlemen,
As a global community, we must invest in peace.
Over the past few months, Ethiopia has made historic investments in peace, the returns of which we will see in years to come.
We have released all political prisoners. We have shut down detention facilities where torture and vile human rights abuses took place.
Today, Ethiopia is highly regarded for press freedom. It is no more a “jailor of journalists”.
Opposition leaders of all political stripes are free to engage in peaceful political activity.
We are creating an Ethiopia that is second to none in its guarantee of freedoms of expression.
We have laid the groundwork for genuine multiparty democracy, and we will soon hold a free and fair election.
I truly believe peace is a way of life. War, a form of death and destruction.
Peacemakers must teach peace breakers to choose the way of life.
To that end, we must help build a world culture of peace.
But before there is peace in the world, there must be peace in the heart and mind.
There must be peace in the family, in the neighborhood, in the village, and the towns and cities. There must be peace in and among nations.
Excellencies, ladies, and gentlemen:
There is a big price for enduring peace.
A famous protest slogan that proclaims, “No justice, no peace,” calls to mind that peace thrives and bears fruit when planted in the soil of justice.
The disregard for human rights has been the source of much strife and conflict in the world. The same holds in our continent, Africa.
It is estimated that some 70 percent of Africa’s population is under the age of 30.
Our young men and women are crying out for social and economic justice. They demand equality of opportunity and an end to organized corruption.
The youth insist on good governance based on accountability and transparency. If we deny our youth justice, they will reject peace.
Standing on this world stage today, I would like to call upon all my fellow Ethiopians to join hands and help build a country that offers equal justice, equal rights, and equal opportunities for all its citizens.
I would like to especially express that we should avoid the path of extremism and division, powered by politics of exclusion.
Our accord hangs in the balance of inclusive politics.
The evangelists of hate and division are wreaking havoc in our society using social media.
They are preaching the gospel of revenge and retribution on the airwaves.
Together, we must neutralize the toxin of hatred by creating a civic culture of consensus-based democracy, inclusivity, civility, and tolerance based on Medemer principles.
The art of building peace is a synergistic process to change hearts, minds, beliefs and attitudes, that never ceases.
It is like the work of struggling farmers in my beloved Ethiopia. Each season they prepare the soil, sow seeds, pull weeds, and control pests.
They work the fields from dawn to dusk in good and bad weather.
The seasons change, but their work never ends. In the end, they harvest the abundance of their fields.
Before we can harvest peace dividends, we must plant seeds of love, forgiveness, and reconciliation in the hearts and minds of our citizens.
We must pull out the weeds of discord, hate, and misunderstanding and toil every day during good and bad days too.
I am inspired by a Biblical Scripture which reads:
“Blessed are the peacemakers, for they shall be called the children of God.”
Equally I am also inspired by a Holy Quran verse which reads:
“Humanity is but a single Brotherhood. So, make peace with your Brethren.”
I am committed to toil for peace every single day and in all seasons.
I am my brother’s keeper. I am my sister’s keeper too.
I have promises to keep before I sleep. I have miles to go on the road of peace.
As I conclude, I call upon the international community to join me and my fellow Ethiopians in our Medemer inspired efforts of building enduring peace and prosperity in the Horn of Africa.

Ethiopian Prime Minister Abiy Ahmed receives Nobel peace prize


ኢትዮጵያዊቷ ፍረወይኒ መብራህቱ የዓመቱ የCNN ጀግና ተብላ ተሸለመች







ኢትዮጵያዊቷ ፍረወይኒ መብራህቱ የዓመቱ የCNN ጀግና ተብላ ተሸለመች፡፡
ፍረወይኒ መብራህቱ ሽልማቱን ያገኘችው ዳግም አገልግሎት ላይ የሚውል የሴቶች ንፅሕና መጠበቂያ ምርቶችን በማቅረቧና ላለፉት 13 ዓመታት በሴቶች የወር አበባ ላይ ያለውን የተሳሳተ አመለካከት ለማረም የሚያግዙ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች በመስራቷ መሆኑን የCNN ዘገባ ያሳያል።
ፍረወይኒ CNN የተባለዉ የአሜሪካ የቴሌቭዥን ጣብያ የ2019 ዓ.ም የአለማችን 10 ጀግኖች ብሎ ከመረጣቸው እጩዎች መካከል አንዷ ሆና የቆየች ሲሆን፤ በዛሬዉ ዕለት ደግሞ አሸናፊ መሆኗን የቴሌቪዥን ጣቢያዉ አስታዉቋል።
ዳግም አገልግሎት የሚሰጡት የሴቶች ንፅሕና መጠበቂያ ምርቶች በመቐለ በሚገኘው ማርያም ሳባ ተብሎ በሚታወቅ ማምረቻ ተቋም ተመርተው በኢትዮጵያ ትግራይ፣ አማራ፣ ኦሮሚያ፣ ደቡብና አፋር ክልሎች ለሚገኙ ሴቶች ይደርሳሉ። እስካሁን ድረስም ለአንድ ሚልዮን ገደማ በገጠሩ የኢትዮጵያ ክፍል ለሚኖሩ እንዲሁም በዝቅተኛ የኢኮኖሚ ዓቅም ላላቸው ልጃገረዶች ከበጎ አድራጊ ተቋማት ጋር በመተባበር በነፃ አቅርባለች፡፡ ሲል የመቀሌዉ ወኪላችን ሚሊዮን ኃይለስላሴ ዘግቧል።
በዚህም ሴት ተማሪዎች በወር አበባ ወቅት ከትምህርት ገበታ የመቅረት አጋጣሚ እንዲሁም ሌሎች ተዛማጅ ችግሮች መቀነሳቸውን ጥናቶች ያመለክታሉ።
ፍረወይኒ ውድድሩን በማሸፏ የ100 ሺህ የአሜሪካን ዶላር ተሸላሚ ሆናለች፡፡


DW AMHARIC

Wednesday 6 November 2019

የኢትዮጵያ ልጅ መሆን ደግሞ የምር ከባድ ነው


በዕውቀቱ ስዩም

መኖር ቀላል አይደለም! የኢትዮጵያ ልጅ መሆን ደግሞ የምር ከባድ ነው፤ የምር! አገር ቤት የሚኖርው አብዛኛ ው ሰው ስራ የለውም! ቁርስ ካገኘ ምሳን ሸውዶት ያልፋል ፤ቤት የለውም፤ ከሁሉ በላይ ሰላም የለውም፤አገሩ ካሁን አሁን በላየ ላይ ፈረሰ እያለ በስጋት ይኖራል

አገሩ ውስጥ ያለው ሃብት ጥቂት ነው፤ ጥቂቱንም ሃያላን ይቀራመቱታል፤ ባገር ውስጥ ያለውን ሀብት በዶሮ ወጥ ብንመስለው ፤ መንግስት “ፈረሰኛውን “ ይበላል፤ ዋናው ሽፍታ መንግስትን አስቦክቶ “ ቅልጥም “ ይደርሰዋል ፤ ለህዝቡ “ ክንፍ “ ይወረውሩለታል ፤ የግዜሩ ወኪል ነኝ እሚለው ሰውየ ደግሞ ፤ ህዝቡ የደረሰውን ክንፍ “ ባርኬ ልመልስልህ” በሚል ሰበብ ወስዶ ይበላበታል! ህዝብ ሲያጉረመርም “ አይዞህ! የሚራቡ ብጡአን ናቸው ይጠግባሉና! በማያልፈው አለም ቅልጥምና ፈረሰኛ እየዘነበልህ ትኖራለህ “ ብሎ ያፅናናዋል! 

የህዝቡ የኑሮ ድርሻ ዶሮ ማርባት ነው ፤ ከዚያ የተረፈውን እድሜውን “ቅልጥሙ” እሚገባው ለሽፍታው ነው ወይስ ለመንግስት የሚል አጀንዳ ፈጥሮ እየተከራከረ፤ አልፎ አልፎ እየተደባደበ ኖሮ ይሞታል! 

ውጭ እሚኖረው ያገር ሰው ስራ አለው፤ ንብረቱ በባንክ፤ ደህንነቱ በፖሊስ ይጠበቅለታል ! ህይወቱ ስራ ነው! እረፍት የለውም፤ በስልኩ ደወል ተቀስቅሶ ለስራ ይሰማራል ! አውቶብስ ውስጥ እየተኛ ፌርማታ አልፎ ይወርዳል፡፡
እየፈጋ ለወንድሙ ይልካል፤ወንድምየው በተላከለት ገንዘብ ይጠብስበታል፤ዲቃላ ይወልድበታል፤ ከዛ ዲይስፖራው፤ ለወንድሙየው ቢራ፤ ለልጅየው ደግሞ ወተት በመግዛት ይጠመዳል ! አላማው ከለታት አንድ ቀን አገር ቤት ገብቶ፤ የሆነ ቢዝነስ ከፍቶ፤ የጦቢያን ፀሃይ እየሞቀ ፅድት ብሎ ለመኖር ነው! ከዚያ አንድ ቀን ገላውን ሲታጠብ ሳሙና አድጦት ባፍጢሙ ተድፍቶ ይገላገላል ! ፅድት ብሎ መኖር ባይሳካለትም ፅድት ብሎ ይሞታል፤ 

አንዳንድ ሰዎች ከድህነት ስለመውጣት እንደቀላል ሲሰብኩ ያስገርመኛል! በድሃነት መውጣት በጣም ከባድ ነው፤ የድሃነት ቅርንጫፉና ስሩ ረጅምና ጥልፍልፍ ነው፤ “ሞ ሰፈር” እሚባል የሴተኛ አዳሪዎች ሰፈር ነበር ፤ በዛ የምትኖር እንዲት ሴትዮ ያካባቢውን ወንዶች ስታስደስት ኖረችና ሞተች ፤ከመሞቱዋ በፊት እድሜ ልኩዋን የለፋችበትን አምስት ሺህ ብር ለብቸኛ ልጁዋ አወረሰችው ፤ ከሰልስቱ በሁዋላ፤ ጎረምሳ ልጅ ከናቱ የወረሰውን ገንዘብ ይዞ እዛው ሴተኛ አዳሪዎች ጋር መጨፈር ጀመረ፤ ይሄንን ያስተዋሉት የሰፈር ሽማግሌ ልጁን ጠርተው “ አንተ ልጅ ይሄ ገንዘብ በእ*ስ መጥቶ በእ*ስ እንዳይሄድ ባግባቡ ያዘው” ብለው መከሩት ይባላል፤ “ ምን እናርግ ተቸገርን “ አለ መንግስቱ ሃይለማርያም! ድህነት ወደ መነሻው እየጎተተን ተቸገርን! 

በዛ ላይ የጉልቤዎች እብሪት፤ ለህዝብ ስቃይ ያላቸው ደንታቢስነት ይዘገንናል ፡፤ተስፋ ለማስቆረጥ አይደለም፤ ግን አሁን ባለው ሁኔታ ከመተጋገዝ ከመተዛዘን ሌላ ተስፋ የለንም ፤ አንዱ ሌላው ህይወት፤ ቅመም እንጂ ህመም ለመጨመር ባይሞክር ትልቅ ነገር ነው!

Monday 21 October 2019

"ለውጡ ሐዲዱን ስቷል ብዬ ነው የማምነው" አርቲስት ታማኝ በየነ

ታማኝ በየነ ዘርፈ ብዙ የኪነ ጥበብ ባለሙያ፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች፣ ፖለቲከኛ፣ የቴሌቪዥን ፕሮግራም አዘጋጅና አቅራቢ፣ ኮሜዲያን እንደሆነ ይነገርለታል። ታማኝ በአገሪቷ በነበረው የፖለቲካ ሁኔታ በስደት ወደ አሜሪካ አቅንቶ ለበርካታ ዓመታት የመንግሥትን አስተዳዳር ሲተች፣ ሲቃወም ነበር።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ ወደ ሥልጣን ሲመጡ ከ22 ዓመታት የስደት ኑሮ በኋላ ታማኝ የአገሩን ምድር መርገጡ ይታወሳል። ለውጡን በመደገፍም የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን ያደርጋል።
በቅርቡ አዲስ አበባ ላይ የኢሬቻ በዓል ሲከበር የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚደንት ያደረጉትን ንግግር ተከትሎ አርቲስት ታማኝ በየነ በፌስቡክ ገፁ ላይ ባሰፈረው ሃሳብ የተነሳ የበርካቶች መነጋገሪያ ሆኖ ሰንብቷል። 

አንዳንዶች 'ተደምሮ ነበር ተቀነሰ' የሚሉ አስተያየቶችንም ሰንዝረዋል። ቢቢሲም ይህንና ሌሎች የአገሪቱ ወቅታዊ ፖለቲካን አስመልክቶ ከታማኝ በየነ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ሰዎች ፖለቲከኛ፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች፣ ጋዜጠኛ፣ አርቲስት ይሉሃል። አንተ ራስህን የምታስቀምጠው የትኛው ላይ ነው?
እኔ መቼም ራሴን የምገልፀው በኪነጥበብ ውስጥ ነው፤ ግን ሁኔታዎች ገፉ ገፉና ወደ ፖለቲካ መድረኩ አመጡኝ እንጅ የሕይወቴ መነሻውም ገና የሰባት የስምንት ዓመት ልጅ ሆኜ ሙዚቃ ነው ሕይወቴ።
በእርግጥ ከ1997 ዓ.ም በኋላ ከኪነ ጥበቡ እየራቅኩ ሄድኩ እንጂ አሁንም ራሴን የማየው የጥበብ ሰው አድርጌ ነው። በእርግጥ ሰዎች የሰጡኝ የተለያዩ ማዕረጎች አሉ፤ ግን ራሴን እንደዛ አድርጌ አልገልፀውም።
ወደ ኢትዮጵያ መጥተህ ከተመለስክ በኋላ ብዙም ድምፅህ አልተሰማም። አሁን ምን እየሠራህ ነው?
እንደዚህ ዓይነት ጥያቄ በማህበራዊ ሚዲያም ሆነ በግል ብዙ ይመጣልኛል።
ሁለት ጊዜ ነው ወደ ኢትዮጵያ የሄድኩት። የመጀመሪያው ወደ አገራችሁ ግቡ ሲባል ነው የሄድኩት። 27 ቀን ገደማ ነው የቆየሁት። ያንንም በተለያዩ አካባቢዎች እየተዘዋወርኩ ሥራ ላይ ነው ያሳለፍኩት። በዚያ ጊዜም የተፈጠሩ ችግሮች ነበሩ - የቡራዩ። እርዳታ ለማሰባሰብ ጥረት አድርጌ ነው ወደ አሜሪካ የተመለስኩት።
ተመልሼ አሜሪካ ከመጣሁ በኋላ ደግሞ የጌዲዮና ጉጂ ችግር ተፈጠረ። በዚያ ምክንያት እርዳታ ሳሰባስብ ነበር። እሱ እንዳለቀ ከአሜሪካው ግብረ ሰናይ ድርጅት ወርልድ ቪዥን ጋር በመሆን እርዳታውን ለማድረስ ተመለስኩ።
እዚያም ሄጀ በተለያዩ አካባቢዎች ችግር ለደረሰባቸው ወገኖች እርዳታ ሳደርስ ነበር። የተለያዩ እንቅስቃሴዎች ላይ ነበርኩ። እንግዲህ ይህን አድርጌ የተመለስኩት ሰኔ መጀመሪያ ላይ ነው። ጠፋህ የምባለውም ለአራት ወር ያህል ነው። ይሄ አራት ወር ደግሞ በጣም ፈተና ውስጥ ያለፍኩበት ጊዜ ነው።
በጣም በቅርብ የማውቃቸው ዶክተር አምባቸውና የሌሎቹም በዚያ መልክ ሕይወታቸውን ያጡት የአማራ ክልል ባለሥልጣኖች ሞት ለእኔ እንደ ሰው በጣም ከባድ ሃዘን ነበር። እንደዚህ ዓይነቱ ሁኔታ በአካባቢው የፈጠረው የፖለቲካ ትርምስም ቀላል አልነበረም።
ከዚያ እንደገና በኢሳት ጊዜያዊ ኃላፊነት ላይ ነበርኩና በውስጡ የተፈጠረውን ችግር ለማርገብ ብዙ ጥረት አድርጌ ነበር። ስመለስ ሁኔታዎች እንደጠበቅኳቸው አልሆኑም። በዚያ ምክንያት እንግዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው ዛሬ የምናገረው፤ ኃላፊነቴን ለቅቄ ወጥቻለሁ።
በዚህ ምክንያት ተደራራቢ የሆኑ የመንፈስም፤ የስሜት መጎዳትም ደርሶብኛል። ምክንያቱም ያን ሚዲያ በእግሩ ካቆሙት ውስጥ አንዱ ነኝ። ስድስት ዓመት በሙሉ አንድም የእረፍት ቀን ቤቴ አሳልፌ አላውቅም፤ ልጆቼን በአግባቡ በእረፍት ቀን አይቻቸው አላውቅም።
ለስድስት ዓመታት ዓለምን እየዞርኩ፤ እየለመንኩም [በዚህ ቋንቋ መናገር እችላለሁ] ያቋቋምኩት ድርጅት ፊቴ ላይ እንደዚህ ዓይነት ችግር ሲገጥመው በጣም ተጎድቼ ነበር እና ኃላፊነቴንም ለቅቄያለሁ።
በራስህ ፈቃድ ነው የለቀቅከው?
አዎ በራሴ ፈቃድ ነው የለቀቅኩት። እንደማይሆን ሳውቅ መልቀቅ ነበረብኝ። ሌላ ተጨማሪ ጉዳት፣ ሌላ ጭቅጭቅ፣ ሌላ ውዝግብ ላለመፍጠር ስል ነው በዝምታ እስካሁን ድረስ የቆየሁት።
አገር ቤት ከመግባታችን በፊት በየጊዜው በአገሪቱ ፖለቲካ ጉዳይ ላይ በኢሳት ላይ እየወጣሁ ሃሳቤን እገልፃለሁ፣ እከራከራለሁ፣ መረጃዎችን አቀርባለሁ። በተጨማሪም በየቦታው ሄጀ በምናገራቸው ንግግሮች በየጊዜው ሃሳቤን ስለምገልፅ ያ በመቋረጡ ምክንያት ነው ብዙ ሰው ጠፋህ የሚለው።
እኔ አሁንም በአገሬ ጉዳይ ላይ አቅሜ የሚችለውን እያደረኩ ነው ያለሁት። ምንም የተደበቅኩበት፤ የጠፋሁበት ምክንያት የለም።
አሁንም ስለ አገርህ የሚሰማህ ስሜት ይኖራል ብ አስባለሁሃሳቤን የምገልፅበት መንገድ አጣሁ ብለህ ታስባለህ?
አጣሁ ማለት አልችልም። ለምን አጣለሁ? ግን እንደበፊቱ . . . አየሽ እዚያው ነው የምሠራው፤ አዳሬ ኑሮዬ ማለት ነው። የተፈጠሩ ሁኔታዎችን በየቀኑ በኢሳት ስለምናገር ነው። አጣሁ ለማለት አልችልም። ይሄን ግን በሌላ በኩል እየሄድኩም እባካችሁ አነጋግሩኝ አልልም።
እኔ መፃፍ አልችልም፤ ተፈጥሮዬም አይደለም፤ ስሜቴንም አይገልፅልኝም። ግን በሚዲያ ደረጃ በዚህ ሃሳብ፣ በዚህ ጉዳይ. . . ያለኝ ማንም የለም። ስለዚህ በዚያ ምክንያት አልታየሁም እንጅ በየቀኑ የሚለዋወጠውን የኢትዮጵያ ፖለቲካ ተደብቄ አይደለም ያለሁት።
አሁን ደግሞ አንዳንድ ችግሮች ሲፈጠሩ፤ ተከፍቶ በነበረው በር እየገባሁ ለምን ይሄ ሆነ? እንዴት እንዲህ ሊሆን ቻለ? የሚል ጥያቄ አቀርብ ነበር። እስካሁን እሱም አልተዘጋም ነበር ለማለት ነው።
ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አስተዳደር መምጣት በኋላ ያለውን የኢትዮጵያን የፖለቲካ ሁኔታ እንዴት ትመለከተዋለህ?
እንግዲህ ለውጥ መጥቷል ብሎ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ዜጋ እ . . . የዛሬ ዓመቱን ሙቀት መለኪያ ባይኖረንም በእርቅና መቻቻል፤ ያለፈውን በመተው ወደፊት ለመራመድ፤ አብሮ ለመጓዝ የሚሉት ሃሳቦች ሁሉም ኢትዮጵያዊ ተቀብሎት ነበር ማለት እችላለሁ። ሁሉም የሚለው ባያስማማን እንኳን 90 በመቶ ብንል ለእውነት የቀረብን ይመስለኛል።
ዶክተር ዐብይ ለዘመናት የሄድንበትን የመበቃቀል ስህተት 'በአዲስ መንፈስ በይቅርታ እንሻገር' ሲል እንደማንኛውም ዜጋ እኔም ደስ ብሎኝ ይሄን ሃሳብ ተቀብያለሁ። ይሄ እንግዲህ የሚሆነው 'ኢትዮጵያ የሄደችበትን የመከራ ዘመን በማሰብ አንድ ቦታ ላይ እንዘጋዋለን' የሚል እንደ አንድ ዜጋ እምነት ስለነበረኝ ነው።
አሁን ያሉትን ሁኔታዎች ስንመለከት በብሔር ተኮር ፖለቲካ ያሉ ኃይሎች ጫፍ እየወጡ ኢትዮጵያዊ የሚለውን የዜግነት ሃሳብ እየገፉ፤ ዜጎች እንደልባቸው እንደ ዜጋ የሚኖሩበትን እያፈረሱ የመገፋፋትና የማፈናቀል. . . እንዲህ ዓይነት ሁኔታ ተፈጥሯል።
ይህ ሊታረም የሚችልበትን መንገድ እንደ አንድ ዜጋ በግሌ ሞክሬያለሁ ሊሰሙኝ የሚችሉ ባለሥልጣናትን ምን እያደረጋችሁ ነው? ብዬ ጮኼያለሁ፤ አዝናለሁ ይህን ስናገር ግን ተስፋ ሰጪ አይደለም። ያሰብነው ጋር እየሄድን አይደለም። ለውጡ ሐዲዱን ስቷል ብዬ ነው የማምነው።
ስለዚህ ጠቅላይ ሚኒስተር ዐብይ ሥልጣን ሲረከቡ የገቧቸውን ቃል እየፈፀሙ አይደለም ብለህ ነው የምታስበው?
መሬት ላይ ባለው ሁኔታ አዎ! ምክንያቱም ዶክተር ዐብይ በኢትዮጵያ ውስጥ አዎንታዊ፤ በተለይ የእናቶችን እንባ የሚጠርግ መንፈስና ሃሳብ ይዞ መጥቷል ብዬ ነው የማምነው፤ የተቀበልኩትም እንደዛ ነው።
አሁን ግን አክራሪ ብሔረተኞች የፈለጉትን የሚያደርጉበት፣ ዜጎች እንደ ዜጋ በነፃነት ሊንቀሳቀሱ የማይችሉበት ሁኔታ ላይ ሲደርሱ ዶክተር ዐብይ ያላቸውን ሥልጣን እና አቅም ተጠቅመው የማስቆም ሥራ እየሠሩ አይደለም።
ይሄ ደግሞ አገሪቷን ወደ ከፋ ደረጃ ይገፋታል ብዬ አምናለሁ። ስለዚህ በእንዲህ ዓይነት ምስቅልቅል ሕይወት ውስጥ ነው ያለችው-አገሪቷ።
ትናንት በሙሉ ልብ ሁላችንም ለመደገፍ የቆምነውን ያህል አሁን አብሮ ለመቆም አስቸጋሪ ሁኔታ እየተፈጠረ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ የላም ኖቤል ተሸላሚ በመሆናቸው ምን ተሰማህ?
ዶክተር ዐብይ የሠላም ኖቤል ሽልማት አሸናፊ ሆኑ ሲባል እኔም እንደ ዜጋ፤ አገሬ በዚያ ክብር ላይ በመጠራቷ ደስ ብሎኝ 'እንኳን ደስ አለዎት' ብያለሁ።
24 ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ደግሞ በዜግነት የሚንቀሳቀሱ ዜጎች 'በአገራችን እኩል ድምፅ የለንም' ብለው ተቃውሞ ለማሰማት ሲንቀሳቀሱ፤ ሲከለከሉና ሲታሰሩ፤ በሌላ በኩል እርሳችውን የሚደግፉ ደግሞ በይፋ . . . ይሄ በፍፁም በፍፁም ሊያኗኑረን የሚችል አይደለምና መስመር ስቷል።
ዶክተር ዐብይ እንደገና ቁጭ ብለው አይተው፣ አስበው፤ ለውጡን በምን መልኩ ላካሂድ የሚለውን ከሁሉም የኢትዮጵያ ባለድርሻዎች ጋር መምከር ካልቻሉ በስተቀር ስለኢትዮጵያ ሁኔታ አሁን በተመለከተ መጥፎ ዕይታ ነው ያለኝ።

ለውጡ አቅጣጫውን ሲስት ስለተመለከትክ የተለያዩ ጥረቶችን እንዳደረክ ነግረኸኛል። ምን ድረስ ነው ጥረት ያደረከው?
ይሄን ነገር መናገር አይከብድም ብለሽ ነው? መቼም በጣም ጥሬያለሁ ብዬ አስባለሁ። እውነቴን ነው የምልሽ ከእርሳቸው ጀምሮ ወደ ታች እስካሉት ባለሥልጣናት ድረስ ምንድን ነው ይሄ ነገር? እያልኩ ጮኼያለሁ፤ በሌላ በኩል ዝም አልክ የሚለኝ ሰው ቢኖርም፤ ዝም ግን አላልኩም። በእያንዳንዱ ጉዳይ ላይ ለመናገር ሞክሬያለሁ።
አንዳንዴ ተመቸንም ብለን፣ ሁኔታው ስለፈቀደልንም፤ በውጭ ስለምንኖርም በማህበራዊ ሚዲያ የምንሰጣቸው አስተያየቶች አልፈው ሄደው በሰው ሕይወት ላይ ጉዳት ሊያደርሱ እንደሚችሉ የተረዳንም አይመስለኝም እና ብዙ ውጥንቅጡ የጠፋበት አሠራር ነው ያለው። ይሄ መታረም አለበት።
በፍትህ ሥርዓቱ ትናንት ያለቀስነውን ያህል ዛሬም የ28 ቀን ቀጠሮ፣ የ18 ቀን ቀጠሮ እየተባለ ዜጎች እንደዛ ሲሰቃዩ ማየት ከዚህ በኋላ እንዲቀጥል እኔ እድል አልሰጥም።
ጠቅላይ ሚነስትሩ ምን ማድረግ አለባቸው ነው የምትለው?
በኢትዮጵያዊ መንፈስ እንደ አንድ አገር ዜጎች አብረን እንኖራለን፤ በመከባበር፣ በመፈቃቀድ እና ቂምን በመተው ይሄን መንፈስ ሲያነሱ በአብዛኛው የተቀበላቸው እኮ የዜግነት ፖለቲካን የሚደግፉ ወይም ደግሞ በኢትዮጵያዊነት የሚያምነው ኃይል ነው። ያን ኃይል ይዘው አገሪቷን መስመር ማስያዝ ነበረባቸው ብዬ አምናለሁ።
ያ ኃይል አሁን ተገፍቷል። ድምፅ የለውም። ለኢትዮጵያዊነት መብት መታገል የሚያስበው ኃይል የለም። አሁን በብሔር የተደራጁ ኃይሎች ናቸው እንደ ልብ የሚንቀሳቀሱት። ከእሱ ነው የሚጀምረው።
ስለዚህ ኢትዮጵያዊው ኃይል ለእርሳቸው ትልቁ ኃይላቸው መሆን ነበረበት። እሱን የተዉት ነው የሚመስለኝ። በሂደት ይታረማሉ ብዬ የማስባቸው ነገሮች ነበሩ ግን እየታረሙ አይደሉም።
ሕገ መንግሥቱስ ለምንድን ነው ድምፅ እንዲሰጥበት የማይደረገው? በዚህ ዓይነት ሕገ መንግሥት ልንፈርስ በየቦታው ጠመንጃ መወልወል በተጀመረበት አገር እንደ አገር መቀጠል አይቻልም። የሕዝቡን ድምፅ እየሰሙ አይመስለኝም። እየሰሙ ያሉት የብሔርተኞችን ነው።
በመሆኑም በሕገ መንግሥቱና ልዩ ኃይል በሚባለው ላይ ጠንከር ያለ አቋም ይዘው ካልወጡ በስተቀር፤ በዚህ ዓይነት ሁኔታ ኢትዮጵያን የመምራቱ ነገር አደጋ ውስጥ ይገባል ብዬ ነው የማስበው።
በዚህ ዓመት ደግሞ ምርጫ ይጠበቃልአሁን ባለው የአገሪቱ ፖለቲካዊ ሁኔታ ምርጫ ይካሄዳል መባሉን እንዴት ነው የምታየው?
እኔን የሚታየኝ? ባለፈው ሳምንት ውስጥ ከአማራ ክልል የሚመጣ መኪና አዲስ አበባ መግባት የለበትም ተብሎ ወጣቶች መንገድ ዘግተው አትገቡም በሚሉበት፤ በምን ዓይነት መለኪያ ነው በዚያ ክልል ውስጥ እኔ የምፈልገው ሰው ይመረጣል ብዬ የማስበው። በፍፁም ሊሆን አይችልም።
በነፃነት የምትንቀሳቀሽበት አገር አይደለም፤ ከዚያ ብሔር ውጪ ከሆንሽ ነፃነት የለሽም። ዜጎችን በሁለት ዓይነት የሚከፍል - ልዩ ዜጋና መጤ ዜጋ በምንባባልበት. . . ምርጫ ተካሂዶ ዴሞክራሲ ይሰፍናል የሚል ቅዠት የለኝም። በፍፁም ሊሳካ የሚችል አይደለም። ብሔርተኞቹ አንድ ላይ መጥተው በበለጠ አደጋ የሚፈጥሩበት ምርጫ ነው የሚሆነው ብየ ነው የማስበው።
እንኳን ምርጫ ማካሄድ ሕግ ማስከበር ይቻላል ወይ? በሕግ የሚፈለጉ ሰዎች ወደ ክልላቸው ሄደው ከተደበቁ እኮ ማውጣት አይቻልም። በምን ዓይነት ዘዴ ነው ምርጫ የሚካሄደው። እንደዚህ ዓይነት ሕግ ባለበት ምን ዓይነት ምርጫ እንደሚካሄድ አይገባኝም። የሕግ የበላይነት ሲባል ዝም ብሎ አይደለም። መንግሥት ሕግ የማስፈፀም አቅም አለው ወይ? የሚለው ነው መታየት ያለበት።
እና ለውጡን በመደገፍህ ትቆጫለህ?
በፍፁም! ለምን እቆጫለሁ? ምክንያቱም ከማንም በቀረበ ኢትዮጵያ እስር ቤቶች ሲፈፀሙ የነበሩ ግፎችን ከተጎጂዎቹ አንደበት፣ ከተጎጅዎቹ ቤተሰቦች የተካፈልኩ ሰው ነኝ። ዛሬ እነዚያ ተጎጅዎች መፈታታቸው ለእኔ ትልቅ ነገር ነው።
በሌላ በኩል ይነስም ይብዛም፤ በምንፈልገው መልኩ ባይሄድም፤ ዛሬ ሃሳብ መግለፅ የሚቻልባቸው ሚዲያዎች ተከፍተው እያየን ነው። ስለዚህ ለውጡን ብንገፋበትና አጠንክረን ብንሄድ የተሻለ አገር፣ የተሻለ ቦታ መድረስ ስንችል እንደዚህ ወደ ኋላ በመጎተታችን ከመቆጨት በስተቀር ለውጡን በመደገፌ ለአንድ ደቂቃም አልፀፀትም።
ይህን ቃለ ምልልስ እንድናደርግ መነሻ የሆነ፤ የኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዚደንት በኢሬቻ በዓል ላይ አደረጉት የተባለውን ንግግር ተከትሎ በአንተ ስም ፌስቡክ ላይ የሰፈረው መልዕክት የአንተ ነው?
አዎ!
ብዙ ጊዜ አንተ የምትታወቀው ኢትዮጵያዊነትና ሰብዓዊነት በማቀንቀን ነው እና በዚህ መልዕክትህ ለአንድ ብሔር ወገነ፤ 'ተደምሮ ነበር ተቀነሰ' የሚሉ ሃሳቦች ተነስተዋል። 'እንደራጅ' ስትል ምን ማለትህ ነው?
ትክክለኛ ጥያቄ ነው። እኔ እንደራጅ ስል አሁንም ተበታትኖ የሚታየው ስለኢትዮጵያ ግድ የሚሰጠውን ኃይል ነው። እንደ ዜጋ በኢትዮጵያ ውስጥ በእኩልነት መኖር እንችላለን የሚለው ኃይል እየተገፋ ስላለ፤ እየለመንን አይሆንም ተደራጅተን ኢትዮጵያዊነታችንን ማስከበር አለብን የሚል ነው።
ነገር ግን ከኦሮሚያው ፕሬዚደንት ንግግር ጋር ተያይዞ አብረው የተነሱ ነገሮች አሉ። በዚህ በለውጥ ሂደቱ ውስጥ ትልቁ ነገር፤ ትናንትን ይቅር ብለን ወደፊት ለመራመድ ስለተነሳን እንጅ አንድን ሕዝብም ሆነ አንድን ግለሰብ በማጥቃት፣ በጠላትነት በመፈረጅ በሚደረግ እንቅስቃሴ ውስጥ በምንም መለኪያ ቁጭ ብዬ ላየው አልችልም።
ስለዚህ የተደረገው ነገር ስህተት ነው። ማንም ሆነ ማን 'ሰብረናቸዋል . . . እንዲህ አድርገናቸዋል' የሚል የዛቻና የበቀል መንፈስ ያለው ሃሳብ እንኳን የመንግሥት ባለሥልጣን ተራ ዜጋ ሊያደርገው የማይገባ ነው። አንዱ ባለጊዜ ነኝ ብሎ ሰብሬህ እንዲህ አድርጌ የሚል ከሆነ ለማንም አይጠቅምም። ለመጠፋፋት እንዘጋጅ እንደ ማለት ነው።
በሌላ በኩል ከአማራነት ጋር አያይዘውታል። ግን አማራስ ቢሆን . . . በማንም ሕዝብ ላይ እንዲህ ዓይነት በጅምላ ያነጣጠረ ነገር፤ በማንኛውም ጊዜ የፈለጉትን ነገር ሊሉኝ ይችላሉ ግን እቃወማለሁ። ኢትዮጵያዊ ዜጋ መብቱ ሲገፈፍ አሁንም ቆሜ አላይም።
እንደራጅም ስል 'ኢትዮጵያዊያን' ስላልተደራጁ ነው። የተደራጁት እንዲህ ዓይነት የበቀል ፖለቲካ እያራመዱ ነው የሚሄዱት። አሁንም ተበትኖ ያለው ኢትዮጵያዊ ኃይል እንዲደራጅ እፈልጋለሁ።
በአገሪቱ ውስጥ እየታ ያሉትን ነገሮች በመመልከት አንዳንዶች የከፋ ሁኔታ ሊከሰት ይችላል የሚል ስጋት አላቸው። አንተስ ይሄንን ስጋት ትጋራዋለህ?
ለሕዝቡ ማመላከት ያለብን ነገር በጎውን ስለሆነ ይህንን ጨለማውን ነገር ባልናገረው እመርጥ ነበር- ሟርት የሚባለው ዓይነት ስለሆነ።
ነገር ግን ወደ እውነቱ እየተጠጋን ከሄድን፤ በጣም እውር የሚያደርግ፣ የሚያሰክር የአልኮል መጠኑ የማይታወቅ ነው - ብሔርተኝነት፤ ምንም ጥያቄ የለውም ወደዚያ ሊወስደን ይችላል። አሁንም ጫፍ ጫፉን እያየን ነው።
አክራሪ ብሔርተኛ ሲኮን ማሰቢያ አዕምሮን ለሌላ አከራይቶ . . . በቃ ያ ሰው በሚያዘው መንገድ እየሄዱ . . . ግደል ያሉትን መግደል፤ አፍርስ ያሉትን ማፍረስ ነው። እንደ ሰው ቁጭ ብሎ አስቦ በራስ አዕምሮ መከራከር አይኖርምና እኔ አሁን አሁን ያሰጋኛል።
ኢትዮጵያዊያን በጋብቻም በማህበራዊ ሕይወትም የተቆራኙ ናቸው እየተባለ ይነገራል፤ በሌላ በኩል ደግሞ የብሔር ግጭት ይባላል። ምንድን ነው ምክንያቱ ትላለህ?
ፖለቲከኞች ናቸው። በጣም ራስ ወዳድ የሆኑ፣ ከራሳቸው በላይ ማየት የማይፈልጉ፣ ከራስ ክብርና ጥቅም በላይ ማየት የማይፈልጉ ፖለቲከኞች እየገፉት ነው እንጂ ሕዝቡ ውስጥ አሁንም አብሮ መኖሩ ገና አልጠፋም።
ያ መተሳሰብ፣ መከባበር አሁንም አለ። ያ ባለበት እንዲዘልቅ ውሃ የሚያጠጣው፣ የሚንከባከበው ግን የለም። የሚያጠፋውን መንገድ እየገፉበት ነው ያለው።
ቁጠሩ ቢባል እንኳን ሁለት ሺህ የማይሞሉ ፖለቲከኞች ናቸው እኮ ከመቶ ሚሊዮን በላይ የሆነውን ሕዝብ የሚያምሱት። ኃላፊነት የጎደለው የማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀምም ለሚደርሰው ውጥንቅጥ ምክንያት ነው። ትልቅ ኃላፊነት በሁሉም ዜጋ ላይ ነው ያለው።
ስለዚህ አሁን በምታያቸው ነገሮች ወደ ተቃውሞ ልትገባ ትችላለህ?
እንዴ?! በደንብ! እንደ በፊቱ በየኤምባሲው አልጮህም። መደረግ ያለበትን ሠርቶ ማድረግ ነው ብዬ ነው የማምነው እንጂ መቃወሜማ አይቀርም። በዚህ ዓይነት መቀጠል አንችልማ! እና በመሰባሰብ፣ ሥራ በመሥራት፣ በመደራጀት፣ መብታችንን ማስከበር በሚለው በጣም አምናለሁ።
የምትደግፈው የፖለቲካ ፓርቲ አለ?
አሁንማ የት አለ [ሳቅ] ቢኖር ኖሮ እኔስ መች እንደዚህ መከራዬን አይ ነበር። ችግሩ እኮ ያ ነው። ምንም እኮ ድምፃችንን ሊያሰማልን የቻለ ኃይል ባለመኖሩ እኮ ነው የተበተነው።
ሌላኛው የማነሳልህ ትረስት ፈንዱን በተመለከተ ነው። ትረስት ፈንዱ ላይ ያለህ ሚና ምንድን ነው?
በመጀመሪያ እንደተቋቋመ፤ እናንተ እንደዚህ ማድረግ ትችላላችሁ ሲባል፤ የደፈረሰ ውሃ የሚጠጣን ወገን ንፁህ ውሃ ማጠጣት ለእኛ በጣም ቀላል ነው። በጣም! ግን ከ5 ሚሊዮን እኮ አላለፍንም። በዚያው ጭቅጭቅ ጀመርን እና አንዳንዶች ገንዘባችን ለመንግሥት ሄዶ ምናምን እያሉ ይጠይቁኛል፤ ግን ለመንግሥት አልሄደም፤ መንግሥት ከፈለገ መዝረፍ የሚችለው በጣም በቂ ገንዘብ አለው። ያ አምስት ሚሊዮን መጣ አልመጣ. . . ኢትዮጵያ እኮ መርከብና አውሮፕላን የሚጠፉባት አገር ናት።
ከገንዘቡ በላይ ሕብረተሰቡን አንድ ላይ የማምጣት፣ ኃላፊነት መስጠት፣ ባለ ጉዳይ ነኝ እንዲል የማድረግ ነገር ነበር የነበረው። አጭር ማስታወቂያ ሠርቻለሁ። ነገር ግን ብዙም አልተሳተፍኩም።
ለምን?
እሱ እንኳን በሥራ መብዛት ምክንያት ነበር እንጅ በመጥፎ አልነበረም። ግን አሁንም በኅብረተሰቡ መካከል የተፈጠረውን የተበታተነ መንፈስ፤ ዶክተር ዐብይ እንዴት እንደሚያስተካክሉት አላውቅም። ካላስተካከሉት ብዙ ውጤታማ ይሆናል ብዬ አላስብም።
በዓለም አቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያ [ Global alliance] በተለይ ከምዕራብ ጉጂ ለተፈናቀሉት እርዳታ ስታሰባስብ ነበር። የትብብሩም ሊቀመንበር ነህ አሁን ምን እየሠራችሁ ነው?
በጌዲዮ ጉጂ ዞን ተፈናቅለው ለነበሩት ቤቶች አሠርተናል። ያ እንዳለቀ በይፋ ይመረቃል። ከዚህ በፊት የሠራናቸው ብዙ ሥራዎች አሉ። በቀደመው ሥርዓት ከእኛ ጋር መገናኘትና ስልክ መደዋወል ክልክል ስለነበር በጣም በጥንቃቄ የዜጎችን መብት ለማስከበር በርካታ ነገር እናደርግ ነበር።
የአካል ጉዳት የደረሰባቸውን ማሳከም፣ ልጆቻቸውን ላጡ ማቋቋሚያ መስጠት፣ ጋዜጠኞች ሲሰደዱ ለእነሱ ድጋፍ ማድረግ ብዙ ሥራ ሠርተናል። አሁን ምን እናድረግ? በሚለው ላይ ለመነጋገር በሚቀጥለው ወር ላይ ጉባዔ አለን። በኢትዮጵያም ተመዝግበን ለመንቀሳቀስ እየሠራን ነው።
እንድንቋቋም መነሻ የሆነን በሳዑዲ በዜጎች ላይ የደረሰው በደል ነበር። አሁን ላይ ጊዜያዊ እርዳታ እየሰጠን መቀጠል እንችላለን ወይ? የሚለውን በደንብ አጥንተን መተዳደሪያ ደንባችንን አስተካክለን ለመንቀሳቀስ እሞከርን ነው።