Monday 7 July 2014

የካምብሪጅ ጠበቆች ቡድን ከእንግሊዝ ውጪ ጉዳይ ባለስልጣናት ጋር ነገ በአንዳርጋቸው ዙሪያ ይሰበሰባል

ኢትዮጵያውያን ጫናቸውን መቀጠል አለባቸው፡፤ እንበርታ ።

አንድአርጋቸው ቴዲ አፍሮ ወይንም ብርቱካን ሚደቅሳ አይደለም !!!ወያኔዎች አንዳርጋቸውን አስረው የፖለቲካ ትርፍ የሚያገኙ መስሏቸዋል። አንዳርጋቸው ሳይታሰር ከሚፈጥረው ተጽእኖ ይልቅ ታስሮ የሚፈጥረው ተጽእኖ ቀላል አይደለም ፡ በውጪ ከሚታገለው እጥፍ በላይ በወህኒ በሚከፍለው መስዋትነት በወያኔ ላይ ትልቅ ተጽእኖ ይፈጥራል።
አንዳርጋቸውን በማሰራቸው የሚጸጸቱበት ቀን ሩቅ አይደለም ። ወያኔ ዝም ያለው የህዝብን ቁጣ በመፍራት ሲሆን በሚስጥር የተበተኑ ደህንነቶች የሕዝቡን ትኩሳት እየለኩ መሆኑን ታውቋል፤ ሃይለማርያም ደሳለኝም ሆነ ሌሎች የወያኔ ባለስልጣናት የአንዳርጋቸውን መታፈን የሰሙት ከግንቦት ስባት መግለጫ መሆኑ ተረጋግጧል። የወያኔ ድህረ ገጾች ላለፍት 2 ሳምንታት ዝምታን መርጠዋል፡ ይህ የሚያመለክተው ወያኔ በራስ መተማመኑ ምን ያህል እንዳጣ ነው፡ ይህ ማለት ፕሮፌሰር አስራትን የያዙበት ግዜ አይነት አይደለም ዘመኑ አሁን የበሰለ ነው ሲሉ መረጃውን ያመጡት ተናግረዋል።
ነገ የሚሰበሰበው የካምብሪጅ የጠበቆች ቡድን ለ እንግሊዝ የውጪ ጉዳይ ሚንስቴር ከባድ እና ህጋዊ ማስጠንቀቂያ በመስጠቱ ይህንን እንደሚያደርግ የሚጠብቀው ቢሮው የጠበቆቹን ቡድን አስከትሎ ክፍተኛ ሚኒስትርን ወደ አዲስ አበባ ይልካል ፤ በእንግሊዝ የሚገኘው ታዋቂ የካምብሪጅ የጠበቆች ቡድን ከባድ ማስጠንቀቂያ ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሰጥቷል።
በመላው አለም የምንገኝ ኢትዮጵያውያን እስከድል ጫፎች ድረስ ጫናችንን መቀጠል አለብን ።

No comments:

Post a Comment