Monday 16 May 2016

ኮደሚኒየሙ ተገኝ



ጠፋ እንዴ!!!
አመት አይሞላኝም ይህንን ........ስሰማ
አንድ የትምህርት ተቋም ህንፃዎች ጠፋበት
ተብሎ ሲታማ
ቢፈለግ.........ቢፈለግ አልተገኘም አሉ
በራሳቸው ቋንቋ "ህንፃ ተሰዊሩ" ብለው
ፎርም ሞሉ
ታዲያ ምን ይደረግ......ከተሰወራቸው
የራሳቸው ጉድፍ ፈልጎ ...... ለማግኘት
ከከለከላቸው
..........................
ኧረ በዚህ ሳምንት ሌላም ሰምቻለው
80 ...ብሎኮች የገቡበት ጠፋ ካየህ
ተብያለው?
በርግጥ ......................አይቻለው
በላንድ ክሩዘር ወደ ላይ ወደ ታች ሲሉ
አስተውያለው
ግን ሰዎች መስለውኝ ተደናግሬአለው
አሁን ግን ገብቶኛል......ተረድቸዋለው
ለካ ....ተቆልሎ ሰው መስሎ ያየነው
በጥቁር..... መስታወት የተሸፋፈነው
የባለ....አራት ፎቁ የጆሞ ህንፃ ነው!!
ታዲያ መቼ ጠፋ ማነው የለም.... ..ያለው
በዝግመተ ለውጥ ወደ 'ቶዮታነት' ተቀይሮ
እኮ ነው
የብሎክ ቁጥሩ..............በታርጋ ተተካ
አስቀያሚው ቀለም ልክ እንደ ፈንዲሻ ነጣ
ብሎ ፈካ
እንደዚህ...........እኮ ነው ለውጡ የተሳካ
መቼም ይኼን ነገር መረዳት ቀላል ነው
ምን ያለውን ነገር..... ምን ካላለው ጋራ
ካላቀላቀልነው
ይልቅ እንዳተኙ ..........እያዳመጣችሁ
በዚህ ከቀጠለ ''ሃገር
ተሰዊሩ"ይደርሳል ጆሯችሁ

Shimelis Tadesse

1 comment: