Tuesday 31 March 2020

የጤና ባለሙያዎች ራሳቸውን ከኮሮና ቫይረስ እንዲጠብቁ የሚለበስ ልብስ (PPE) ያዘጋጀው ወጣት ኢትዮጵያዊ ኢንጂነር!

የጤና ባለሙያዎች ራሳቸውን ከኮሮና ቫይረስ እንዲጠብቁ የሚለበስ ልብስ (PPE) ያዘጋጀው ወጣት ኢትዮጵያዊ ኢንጂነር!
.
የማስተዋውቃችሁ ኢንጂነር ሳሮን ለሁሉም አርአያ መሆን የሚችልና ሊደገፍ የሚገባው ወጣት ነው። ይህ የምታዩት ልብስ በራሱ ተነሳሽነት ጥናት አድርጎ ፣ በራሱ ወጪ ያዘጋጀው ነው። ለቫይረሱ ይበልጥ ተጋላጭ የሆኑ ጤናው ላይ የሚሰሩ ያገሩን ልጆች ለማገዝ ካለው መልካም ሐሳብ ነው ይህን ያደረገው። በፎቶው ላይ ለብሶት የምታዩትን አንዱን ልብስ ከውጭ ለማስገባት ከ2,000 እስከ 3,000 የኢትዮጵያ ብር ያስፈልጋል።
.
ኢንጂነር ሳሮን ግን ዋጋውን በ1/4ኛ ቀንሶት በ500 የኢትዮጵያ ብር ገደማ አንድ የፕላስቲክ ልብስ ማዘጋጀት እንደቻለ ነው የነገረኝ። ከተማሩ አይቀር እንዲህ ላገር መትረፍ ያኮራል።
.
እሱን ቀጥታ የምታገኙት በስልክ ቁጥሩ 0917807480 ሲሆን ጥያቄ ካላችሁም በኮመንት ልትጽፉልኝ ትችላላችሁ።
.
ዶ/ር ኤልያስ ገብሩ አዕምሮ



No comments:

Post a Comment