Sunday 10 March 2013

መገናኛ ብዙሃን ዋናው መሳሪያችን ነው



የታዋቂው ኢሳት ቴሌቪዢን ጋዜጠኛ የሆነው ጋዜጠኝ ፋሲል የኔ አለም በትናትናው ዕለት ለስራ ጉብኝት በኦስሎ ተገኝቶአል በዚሁ ዕለት  በዲሞክራቲክ ለለውጥ ድጋፊ ሰጪ ድርጅት በኖርዌይ ባደረገለት የአቀባበል ግብዣ ተገኝቶ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እየደረስ ያለውን  የከፋ የህዝብ እና የሃገር ጥፋት ላይ ከአባላት ጋር ሰፊ ውይይት አድርጎል የኢሳት ቴሌቪዝን ጣቢያ ከኢትዮጵያ ህዝቡ በቀን ውስጥ  1000 በላይ የሆኑ የስልክ ጥሪዎችን እንደሚደርሱት እና  በመንግስት የሚደርስባቸውን በደል  ለአለም ህዝብ አሳውቁልን በማለት የተማጽኖ ጥሪ እንደሚያቀርቡ ተናግሮኦል ሃገራችንን ኢትዮጵያ እንደ ሃገር ሆና እንድትቀጥል ተረባርበን ዘረኛውን አገዛዝ ማሰወገጃው ግዜው አሁን ነው መገናኛ ብዙሃን  ዋናው መሳሪያችን ነው   አገዛዙን ለመጣል በሚደረገው ትግል  የህዝብ አይና እና ጆሮ የሆነው ኢሳት እያደረገ ያለው አስተዋጾ በአጭር ጊዜ ውስጥ ነጻነት ያጎናጽፈናል  ሲሉ አባላቶቹ ተናግረዋል በዕለቱም ከፍተኛ የደርጅቱ አመራሮች ተገኝተዋል





No comments:

Post a Comment