Wednesday 11 April 2018

ሰጋጅና አሰጋጅ !


Image may contain: 1 person, sitting




ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ

ይህ ፎቶ በፎቶ ሾፕ የተቀናበረ አይደለም ብዬ ልመን ። እውነት ነው ብለን ካመንን ፣ ተንበርካኪው " ጋዜጠኛ " ከሆነ ስራውን ትቶ ለመስገድና ለማጎብደድ የሚመች ሌላ ስራ ቢፈልግ ያዋጣዋል ። የሙያ ፍቅር ወይም የቦታው አለመመቸት ሊባል መቸው አይችልም ። በዘመኑ ቋንቋ ተንበርካኪነት ነው ። ሰውየው ራሱን ብቻ ሳይሆን የጋዜጠኛን ሁሉ ክብር ይዞ ነው የተንበረከከው ። ከሰጋጁ ደግሞ አሰጋጁ ይደንቃል ። አጠገቡ ሌላው ቢቀር አንደ የሰው ልጅ ተንበርክኮ ( በፈቃዱም ይሁን በምንም ምክንያት ) እንዲህ ተደላድሎ ማውራት መቻሉ ይገርማል ።

ሰውን ለመርገጥም መቻልን ይጠይቃል ። ማንም ድንገት ተነስቶ እንደ ሁለቱም ሰዎች መሆን አይችልም ። ይህ ሙያ የእኔ ሙያ ነው ። የጋዜጠኝነት ሙያ የሕይወት መስዋዕትነት የሚጠይቅ ሙያ መሆኑን አውቃለሁ ። ምንም ሳይቸግር እንዲህ መሆን ግን ክብረ ነክ ነው ። ለሕዝቦች እኩልነት ፣ ለፍትህ ፣ ለዴሞክራሲ በረሀ ግብቶ የታሀለ ሰው ከምቾት በኋላ እንዲህ ሲሆን ማየት ብዙ ጥያቄ ያስነሳል ። ጉዳዩ በዚህ ብቻ አያበቃም ። በአንዲት ነጻና ሉዓላዊት ሀገር ፣ ያውም ለሌላ መስገድን ለማታውቅ ሀገር ይህን ትርዒት ማየት አስደማሚ ነው ። ይሁንና ሁለቱም ሰዎች በአንድ ያልታወቀ ምክንያት ተስማምተዋል ። ይህ ችግር ሳይሆን ስምምነት ነው ።



No comments:

Post a Comment