Thursday 25 October 2018

የኢትዮጵያ የመጀመሪያዋ ሴት ርዕሰ ብሄር - ወ/ሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ፣





Image result for Sahle work zewde Ethiopia president

የካቲት፣ 1942 አዲስ አበባ ውስጥ የተወለዱት ወ/ሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ እድገታቸውም እዚሁ አዲስ አበባ ውስጥ ነው፡፡
ወ/ሮ ሳህለወርቅ የሁለት ወንድ ልጆች እናት ሲሆኑ አማርኛ፣ እንግሊዝኛ እና ፈረንሳይኛ አቀላጥፈው ይናገራሉ፡፡
ከፈረንሳዩ ሞንተፔለ ዩኒቨርሲቲ በተፈጥሮ ሳይንስ የተመረቁት ወ/ሮ ሳህለወርቅ እ.ጎ.አ ከ1989 እስከ 1993 ባሉት ዓመታት ተቀማጭነታቸውን ሴኒጋል ውስጥ በማድረግ የጊኒ ቢሳው፣ የጋምቢያ፣ የማሊ፣ የኬፕ ቨርድ እና የጊኒ አምባሳደር በመሆን ማገልገላቸውን ተመልክተናል፡፡
እ.ጎ.አ ከ1993-2002 በጅቡቲ አምባሳደር ሆነው ሰርተዋል፡፡ በዚሁ ወቅት የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግሥታት ድርጅት (ኢጋድ) ቋሚ ተወካይም ነበሩ።
እ.ጎ.አ ከ2002-2006 በፈረንሳይ አምባሳደር እንዲሁም የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት የሳይንስና የባህል ተቋም (ዩኔስኮ) ተወካይ ሆነው ሰርተዋል።
በመቀጠልም፣ በተባበሩት መንግሥታት ልዩ መልዕክተኛ ውስጥ የተቀናጀው የሰላም አስከባሪ ሃይል ተወካይ በመሆን በሴንትራል አፍሪካ(BINUCA) ኃላፊ በመሆን ማገልገላቸውን ለማወቅ ችለናል፡፡
ወ/ሮ ሳህለወርቅ፣ በአፍሪካ ሕብረት እና በተባበሩት መንግሥታት የኢኮኖሚ ኮሚሽን ውስጥ የኢትዮጵያ ቋሚ ተወካይ በመሆን እንዲሁም በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ውስጥም የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄነራል ሆነው አገልግለዋል፡፡
እ.ጎ.አ በ2011 የተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀሃፊ የነበሩት ባንኪ ሙን፣ በኬኒያ የተባበሩት መንግሥታት ዳይሬክተር ጄነራል አድርገው ሾመዋቸው አገልግለዋል።
ከዚህም በተጨማሪ፣ በተባበሩት መንግሥታት ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬስ በአፍሪካ ሕብረት ልዩ ተወካይ እንዲሁም በአፍሪካ ሕብረት የተባበሩት መንግሥታት ቢሮ ኃላፊ ሆነው ተሹመው እንደነበር ለማወቅ ችለናል፡፡
...
ለምክር ቤቱ ባደረጉት ንግግር፣ በሥራ ዘመናቸው ስለሰላም ትኩረት ሰጥተው እንደሚሰሩ የተናገሩት ርዕሰ ብሄሯ፣ “ሥር የሰደደውን ጥላቻ፣ መናናቅና አልፎ አልፎ የሚታየውን ጠብ በኢትዮጵያዊ ጨዋነት፣ በዳበረ የቤተ እምነቶች ጥበብና የሽምግልና ሥርዓት ከወዲሁ በመግታት ለራሳችንም ሆነ ለትውልድ የምታኮራ ሐገር መፍጠር ይኖርብናል” ሲሉ ተናግረዋል

No comments:

Post a Comment