Saturday 27 October 2012

የአላሙዲን ኪስ በወርቅ ሲታጨቅ፤ አድላ ኑሮ በጭንቅ!


(አሥራደው ከፈረንሳይ)

ተናገር መጋዶ ተናገር ሻኪሶ ፤
ወርቅ ወዴት ተጋዘ ላንተ አፈሩ ደርሶ ፤
ተናገር ሃዱማ ደግሞም ኡላኡሎ ፤
እነማን ዘረፉት የወርቁን አሎሎ ፧፦
የወርቁን ቡችላ የለገ ደንቢውን ፤
ደብዛውን ንገሩን የደረሰበትን ፧፦

እነማን ዘረፉት ፧ ማንስ ከበረበት ፧፦
እነማን ተዝናኑ፧ ማንስ ጨፈረበት ፧፦
ደሃ በደከመ ደሃ በሞተበት ፤
ጦሙን እንደዋለ አፈር ተንዶበት ፥፥

አካፋና ድማ ይዘው ሳይቆፍሩ ፤
ጨለማ መግፈፊያ ሻማ ሳያበሩ ፤
ጠብ ሳይል ላባቸው ባቋራጭ ከበሩ ፡
ያገር አንጡራ ሃብት እየመዘበሩ፥፥

ዕትብቱ ተቆርጦ ለተቀበረበት፤
ለወርቁ ባለቤት ምንም ሳይሰሩሉት ፤
ጉሮሮውን አንቆ ካፉ በመቀማት ፤
ሃብታም መዘበረ ባዳ ከበረበት ፥፥

አወይ ክብረ መንግሥት እንዴት ነው አዶላ ፧፦
ደሃን እያስራበ ሃብታም የሚያበላ ፦

 
 

No comments:

Post a Comment